ኳታር እስራኤልን አወገዘች

Date:

የኳታሩ ኤሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ አል ታኒ  እስራኤል በሶሪያ ላይ የፈጸመችውን ጥቃት ኮንነዋል፡፡

ከሶሪያው ፕሬዚዳንት አህመድ አል ሻርዓ ጋር በስልክ ሲወያዩ ነው አል ታኒ እስራኤልን ያወገዙት፡፡

የእስራኤል ጥቃት የሶሪያን ሉዓላዊነት የጣሰ እና
የዓለም አቀፉን ህግ እንዲሁም የመንግስታቱ ድርጅትን ቻርተር ግምት ውስጥ ያላስገባ ነው ብለዋል ኢሚሩ፡፡

የአል ጁላኒ መንግስት የውስጥ አንድነቱ የተጠበቀ እንዲሆን እና የአገሪቱን ዳር ድንበር በማስከበሩ  ረገድ አቅም ከመፍጠር አንጻር  ዶሃ ከጎኑ እንደምትቆምም አረጋግጠዋል።

ኳታር እስራኤልን እና ሃማስን በማደራደር ከፍተኛ ሚና ያላት አገር በመሆኗ በመካከለኛው ምስራቅ ያላት ተጽዕኖ በቀላሉ የሚታይ እንዳልሆነም ተዘግቧል።

ቀጠናዊ መረጋጋት መፍጠር ኳታር ቅድሚያ የምትሰጠው ጉዳይ ስለመሆኑም በሁለቱ መሪዎች የስልክ ውይይት ወቅት ተወስቷል፡፡

እስራኤል በመሀል ደማስቆ የሶሪያ መንግስት መከላከያ ሚኒስቴር ዋና መስሪያ ቤትን ቤተ መንግስቱ አቅራቢያ መደብደቧ አይዘነጋም ሲል የዘገበው አልጀዚራ ነው፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ቴዲ አፍሮ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ቀይሮታል!” — ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

በ"ወቸው ጉድ" ፖድካስት ላይ እንግዳ ሆነው የቀረቡት ፕሮፌሰር ብርሃኑ...

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...