ወይዘሪት ሜሮን የ3ኛው “መሳላ አዋርድ” አሸናፊ ሆነች

Date:

ወይዘሪት ሜሮን ታደሰ የ2018 ዓ.ም. የ3ኛው “መሳላ አዋርድ” አሸናፊ ሆና መመረጧን “Visit Kambata” የተሰኘው ድርጅት አስታወቀ። ውድድሩ የተካሄደው የከምባታ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል የሆነውን መሳላን ተከትሎ በዱራሜ ከተማ ነው።

ውድድሩ የተዘጋጀው “Visit Kambata” ከከምባታ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ጋር በመተባበር ነው። አሸናፊዋ ሚስ ሜሮን ታደሰ፣ ለሚቀጥለው አንድ ዓመት የከምባታን ባህል፣ ታሪክ እና የተፈጥሮ ጸጋዎች በአገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ የማስተዋወቅ ኃላፊነት እንደተሰጣት አዘጋጆቹ ገልጸዋል።

የ2018 “ሚስ መሳላ” አሸናፊዋ ወ/ት ሜሮን ታደሰ በበኩሏ፣ ለድርጅቱ ላገኘችው እድል ምስጋናዋን አቅርባለች። “የብሔሩን ታሪክ፣ ባህልና የተፈጥሮ መስህቦችን በማስተዋወቅ ኃላፊነቴን እወጣለሁ” ስትልም ቃል ገብታለች።

የመሳላ አዋርድ የከምባታን ብሔር ልዩ የሆነውን የዘመን መለወጫ በዓል ከማድመቁም በላይ፣ ወጣቶች በባህላቸው ላይ እንዲኮሩ እና በማስተዋወቅ ሥራ ላይ እንዲሳተፉ ትልቅ መድረክ እየፈጠረ ይገኛል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...