ዘለንስኪ ከአሜሪካ ጎን ቆሙ፤ በኢራን “ለውጥ ያስፈልጋል” ሲሉ ጥሪ አቀረቡ

Date:

​የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በኢራን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ የአሜሪካን አቋም እንደሚደግፉ በይፋ አስታወቁ። ፕሬዝዳንቱ በሰጡት መግለጫ፣ ለበርካታ ዓመታት የዘለቀውና የብዙ ሰዎችን ህይወት የቀጠፈው የቴህራን አገዛዝ “ሊቀጥል አይገባም” በማለት ጠንካራ ሂስ ሰንዝረዋል።

በኢራን ውስጥ መሰረታዊ ለውጦች መደረግ እንዳለባቸው ያሳሰቡት ዘለንስኪ፣ የሀገሪቱ መንግስት በገዛ ዜጎቹ ላይ እየወሰደ ያለው እርምጃ ተቀባይነት እንደሌለው አመልክተዋል።

​ይህ የፕሬዝዳንቱ መልዕክት የተሰማው፣ በርካታ የአውሮፓ ሀገራት በኢራን የፀጥታ ኃይሎች በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የሚፈጸመውን የኃይል እርምጃ በመቃወም የሀገሪቱን አምባሳደሮች ለውይይት በጠሩበት ወቅት ነው።

የኢራን መንግስት በሰልፈኞች ላይ እየወሰደ ያለው ደም አፋሳሽ እርምጃ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ጫና እያስከተለበት ይገኛል።

​በሌላ በኩል፣ የዩክሬን የጦር ጠላት የሆነችውና የኢራን የቅርብ አጋር ተደርጋ የምትታሰበው ሩሲያ፣ በኢራን የውስጥ ጉዳይ ላይ የሚደረገውን ጣልቃ ገብነት አውግዛለች። ሞስኮ በቴህራን የውስጥ ፖለቲካ ውስጥ የሚታየው እንቅስቃሴ “አፍራሽ የውጭ ጣልቃ ገብነት” ነው ስትል መግለጿ በጉዳዩ ላይ በታላላቅ ኃይሎች መካከል ያለውን የጎላ ልዩነት አሳይቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...