ሃይንከን ኢትዮጵያ – የማኅበረሰብ ድጋፍ- ምርትን በኃላፊነት መጠቀም

Date:

ሃይንከን ኢትዮጵያ የኢትዮጵያን ገበያ ከተቀላቀለበት የአውሮፓውያኑ 2011 ጀምሮ በሺዎች ለሚቆጠሩ በርካታ የሥራ እድል የፈጠረ፣ ማኅበረሰቡን በተጨባጭ የደገፈ፣ በአገሪቱ ሁለተኛ ግብር ከፋይ የሆነ ብሎም በአካባቢ ጥበቃና ምርቶቹ በኃላፊነት እንዲጠጡ የሚሰራ የአገር ሀብት የሆነ ድርጅት ነው፡፡ 

አገርን ማልማት በሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች የላቀ ተሳትፎ ሲደገፍ ዕውን የሚሆን ነው፡፡ በዘመናዊ የንግድ ሥርዓት ውስጥ ደግሞ፤ የአንድ ተቋም ስኬት የሚለካው በአትራፊነቱ ብቻ ሳይሆን ለአገር ኢኮኖሚ እና ማኅበራዊ ልማት በሚያበረክተው አገራዊ አስተዋጽኦ ጭምር ነው፡፡ ይህንንም ሃይንከን በተለያዩ ጊዜያት በተግባር ገልጦታል፡፡ 

ሃይንከን ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ፣ ሐረርና በደሌ በርካታ የማኅበራዊ ድጋፍ ተግባራትን ያከናውናል፡፡ ደራሽ በተሰኘው ለችግረኛ ወገኖች ቤት ገንብቶ የማስረከብ ፕሮጀክቱ እስካሁን በአዲስ አበባና በሐረር ደረጃቸውን የጠበቁ 153 ቤቶችን ሰርቶ ያስረከበ ሲሆን፤ ዘንድሮ ደግሞ ስድስተኛውን የደራሽ ፕሮጀክት በበደሌ ከተማ በማጠናቀቅ 20 ቤቶችን ገንብቶ ለ20 ቤተሰቦች አስረክቧል፡፡ በዚያው በበደሌ በሚገኘው ቢራ ፋብሪካው ከፈጠረው በሺህ የሚቆጠር የሥራ እድል በተጨማሪ በርካታ የከተማዋ ቤተሰቦች በከብት እርባታ፣ በዶሮ እርባታ፣ በምግብና መጠጥ ንግድ ሥራ፣ በመኪና እጥበት አገልግሎትና በመሳሰሉት ዘርፎች እንዲሰማሩ በማድረግ በቤተሰብ ደረጃ ገቢያቸው እንዲዳብር አስችሏል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ በአዲስ አበባና በሐረርም በቤተሰብ ደረጃ ገቢን የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች ተተግብረው ቁጥራቸው ከፍተኛ የሆኑ ወገኖች ተጠቃሚ ሆነዋል፡፡

በ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የግብር ከፋዮች ዕውቅና እና ሽልማት ሥነ ሥርዓት ላይ የሃይንከን ኢትዮጵያ የላቀ የኃላፊነት ስሜትና ቁርጠኝነት በድጋሚ ተንፀባርቋል፡፡ ድርጅቱ ከሁሉም የመንግሥት እና የግል የግብር ከፋይ ድርጅቶች መካከል ከኢትዮ ቴሌኮም ቀጥሎ 18 ቢሊዮን ብር በመክፈልና ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ እና ለሰባት ተከታታይ ዓመት ‹‹ፕላቲነም ግብር ከፋይ›› ሽልማትን በመቀበል ለአገር ዕድገት የጎላ ድርሻ እንዳለው አስመስክሯል፡፡ 

ለአገሪቱ ከፍተኛ ግብር ገቢ ከማድረግ ባሻገር ሃይንከን ኢትዮጵያ በመሠረተ ልማት ግንባታ፣ በትምህርት፣ በጤና እና በሌሎች ወሳኝ የልማት ዘርፎች ላይ የአገሪቱ የኢኮኖሚ አቅም እንዲጠናከር ወሳኝ ሚና ይጫወታል፡፡ ማኅበራዊ ኃላፊትን በመወጣት ዙሪያ የቢራ ምርቶችን በኃላፊነት መጠቀም ላይም ቁልፍ ሥራዎችን ያከናውናል። የተወሰኑትን እንቃኛቸው :-

በልክ በአግባብ ላፊነት

አራዳ ከጠጣ የማይነዳ

ይህ መልእክት በ50 የአዲስ ሜትር ታክሲዎች ላይ ተለጥፎ በአዲስ አበባና ዙሪያዋ ታክሲዎቹ በሚዘዋወሩባቸው ቦታዎች ሁሉ በቀን እስክ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ ይመለከታቸዋል፡፡

የዚህ ዘመቻ አካል የሆኑት ቢጫ ታክሲዎች በተለይ በቦሌ አየር ማረፊያና በአዲስ አበባ እና በአቅራቢያው ባሉ ከተሞች ‹‹ከጠጡ አይንዱ›› የሚል ጠንካራ መልዕክት ላለፉት ሦስት ዓመታት ለተሳፋሪዎችና ለሹፌሮች በማስተላለፍ ላይ ናቸው፡፡ እነዚህ ተሽከርካሪዎች በርካታ ሰዎች ዘንድ በመድረስ ኃላፊነት ስለተሞላበት የአልኮል አጠቃቀም ወሳኝ ውይይቶችን እያነሳሱ ነው፡፡ 

ዘመቻው በይፋ ሲከፈት የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንትን ኤጀንሲ፣ የትራፊክ ፖሊስ፣ የፖሊስ አስተዳደር አካላት፣ የሃይንከን ኢትዮጵያ ማኅበራዊ ተጽዕኖ አምባሳደሮች ተዋናይ ይገረም ደጀኔና ተዋናይት ሸዊት ከበደ እና የታክሲ ሹፌሮችን ጨምሮ፤ የትራፊክ ደህንነትን ለማስጠበቅ የቆሙ ቁልፍ ባለድርሻ አካላትን በሙሉ በአንድነት አሰባስቧል፡፡ ይህ አጋርነት በመንገዶች ላይ የኃላፊነት ስሜትን በማዳበር፣ አሽከርካሪዎች እና እግረኞች ለአደጋ እንዳይጋለጡ አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡ 

በአጠቃላይ፣ የሃይንከን ኢትዮጵያ አገራዊ አስተዋጽኦ ለኢትዮጵያ ልማት ያለው ቁርጠኝነት በከፍተኛ የግብር ከፋይነት ብቻ ሳይሆን፣ የወጣቱን ትውልድ ጤናማ አስተሳሰብ በመቅረጽ፣ የትራፊክ ደህንነትን በማስጠበቅና በአጠቃላይ ለማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት በሚያደርገው የማያቋርጥ ድጋፍ ጭምር የሚንጸባረቅ መሆኑን ያመለክታል፡፡

‘’እድሜዬ ሳይፈቅድ አልኮል መጠጥ አልቀምስም’’

ይህ መርሃ ግበር በየዩኒቨርሲቲው የሚገኙና በተለይም የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች አልኮል አልጠጣም እንዲሉ የሚመከር ዘመቻ ነው፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ወጣት ተማሪዎች ከቤተሰቦቻቸው ተለይተው በሚወጡባቸው የመጀመሪያ ዓመታት ተጋላጭነታቸው ስለሚጨምር በሕግ የተቀመጠውን አልኮል የመጠጣት የዕድሜ ገደብ እንዲያከብሩ የሚያበረታቱ ዘመቻዎች ለአራት ተከታታይ ዓመታት በ12 ዩኒቨርሲቲዎች በተሳካ ሁኔታ ተከናውነዋል፡፡ ይህ ዘመቻ በአራት ምዕራፎች ከ4,500 በላይ  ተማሪዎችን አሳትፏል፡፡ ዘመቻው በተለይ አዲስ ለተመዘገቡ ተማሪዎች ‹‹አልኮል አልቀምስም›› (No for Alcohol) የሚል መልዕክት በማስተላለፍ ላይ የሚያተኩር ሲሆን፤ ተማሪዎቹ ትምህርቴን ሳልጨርስ አልኮል መጠጥም ይሁን ሌሎች ሱስ አስያዥ ነገሮችን አልቀምስም ሲሉ የቃል ኪዳን ሰነድ እንዲፈርሙ ይደረጋል፡፡ መፈረም ብቻም ሳይሆን መተግበራቸውን ከመካከላቸው በተቋቋሙ ቡድኖች አማካኝነት ክትትል ይደረጋል፡፡

በፕሮግራሙ ወቅት መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተወካዮች፣ የሃይንከን ኢትዮጵያ ማኅበራዊ ድጋፍ አምባሳደሮች፣ ባለሙያዎች እና የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር አካላትና ፕሬዚዳንቶች በመገኘት ለወጣት ተማሪዎች ምክር ለግሰዋል፡፡ ከአልኮል ጋር በተያያዘ ሊከሰቱ በሚችሉ ችግሮች ዙሪያም ትምህርትና ውይይት ተካሂዷል፡፡ 

ይህ ዘመቻ በቀጥታ በሃይንከን ኢትዮጵያ የሚካሄድ ሳይሆን በዘርፉ የካበተ ልምድ ባላቸው ተግባሪ አካላት የሚመራ ነው፡፡ በእነዚህ ዘመቻዎች ወቅት ምንም አይነት ሃይንከን ኢትዮጵያ በስፍራው መኖሩን የሚያመላክቱ ተግባራት ወይንም ከቢራ ምርት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች በጭራሽ አይነሱም፡፡ 

የምናድገው ከኢትዮጵያ ጋር ነው!

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የዓለም የቡና ገበያ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱ ተገለጠ

በዓለም አቀፍ ደረጃ በቡና አቅርቦት ላይ ተፈጥሮ የነበረው ስጋት...

አሜሪካ የኢራንን የጭነት መርከብን መያዟን አስታወቀች

በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን የዘጋችው...

“ቴዲ አፍሮ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ቀይሮታል!” — ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

በ"ወቸው ጉድ" ፖድካስት ላይ እንግዳ ሆነው የቀረቡት ፕሮፌሰር ብርሃኑ...