የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ቀደም ሲል ይጠቀምበት የነበረውን ሎጎ (አርማ) በአዲስ መቀየሩን ይፋ አድርጓል።
ኤጀንሲው ይህንኑ አዲስ ሎጎ በማስተዋወቅ አጠቃላይ ተገልጋዮች፣ የሴክተር መሥሪያ ቤቶችና ባለድርሻ አካላት ተቋሙ በታደሰ መንፈስ ለላቀ አገልግሎት መዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡
ይህ የተቋሙ የሎጎ እና የብራንዲንግ (Branding) ለውጥ የውጫዊ ገጽታ መቀየር ብቻ ሳይሆን፣ ኤጀንሲው እያካሄደው ያለው ሰፊ የተቋማዊ ሪፎርም (የለውጥ እንቅስቃሴ) ዋነኛ አካልና ማሳያ መሆኑም አስታውቋል።
ኤጀንሲው ተገልጋዮቹን በታላቅ ትሕትና ለማገልገል ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡
ኅብረተሰቡ አገልግሎት ለማግኘት ወደ ኤጀንሲው ሲመጣ ማንኛውም ዓይነት መጉላላት ቢገጥመው፣ አልያም ሕገ-ወጥ አሠራር ቢመለከት ወይም አስተያየትና ጥቆማ መስጠት ቢፈልግ 6577 የተቋሙ የነጻ የስልክ መስመር በመደወል መረጃ መስጠት እንደሚችል ኤጀንሲው አሳስቧል።
