የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት ለኢትዮጵያዊያን የተለየ ጥበቃ እንዲደረግ አዘዙ

Date:

የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት አብዲራህማን አብዲላሂ፣ የግዛቲቷ ጸጥታ ኃይሎች ለኢትዮጵያዊያን የተለየ ጥበቃ እንዲያደርጉ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውን የግዛቲቷ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ፕሬዝደንቱ ይህን ትዕዛዝ የሠጡት፣ ሰሞኑን ሐርጌሳ ውስጥ በአንድ ኢትዮጵያዊ ወጣት ላይ የተወሰኑ ግለሰቦች ማስፈራሪያና ዛቻ ሲያደርሱ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል መሠራጨቱን ተከትሎ ነው።

ፕሬዝዳንቱ፣ ሶማሌላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ሥር የሰደደ ግንኙነት እንዳላት መናገራቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

የፕሬዝዳንቱን ትዕዛዝ ተከትሎ፣ ጸጥታ ኃይሎች አብዲሪሳቅ ሙሴ የተባለ በቲክቶክ ላይ በተለይ የኦሮሞ ብሄር ተወላጆች የጥቃት ሰለባ እንዲኾኑ ሲቀሰቅስ ነበር የተባለ ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውለዋል መባሉን ዋዜማ ዘግባለች።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...