የትራምፕ አስተዳደር አዲስ የተማሪ ቪዛ ቀጠሮዎችን አገደ

Date:

የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር የአሜሪካ ኤምባሲዎች ለዓለም አቀፍ ተማሪዎች አዲስ የተማሪ ቪዛ ቀጠሮ መስጠት እንዲያቆሙ ትእዛዝ አስተላልፏል።

በአሜሪካ ለመማር ያሚያመለክቱ ሰዎችን የማህበራዊ ሚዲያ መረጃ በጥልቀት ለመፈተሽ በማሰብ አስተዳደሩ ይህን መመሪያ ማስተላለፉ ነው የተገለጸው።

የተፈረመው ይህ መመሪያ ለሁሉም የአሜሪካ ኤምባሲዎች እና ቆንስላዎች መላኩን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ አስታውቀዋል።

መመሪያው የሀገሪቱ መንግስት በዓለም አቀፍ ተማሪዎች ላይ ከወሰዳቸው በርካታ እርምጃዎች አንዱ ሲሆን እነዚህ እርምጃዎች የተማሪ ቪዛን መሰረዝ እና የውጭ ተማሪዎች እንደ ሃርቫርድ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች እንዳይመዘገቡ መከልከልን ያካተታል።

የትራምፕ አስተዳደር መመሪያው የተላለፈው የሀገርን ደህንነት ለመጠበቅ እና ሽብርተኝነትን ለመከላከል ነው ሲል ገልጿል።

በሌላ በኩል የዓለም አቀፍ መምህራን ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ ፋንታ አው “ዓለም አቀፍ ተማሪዎች ስጋት አይደሉም” ሲሉ ውሳኔውን ተችተዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለውም መመሪያው ተማሪዎች ወደ አሜሪካ እንዳይመጡ ተስፋ ሊያስቆርጥ እና በዩኒቨርሲቲዎች ላይ የገንዘብ ተጽዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል አሳስበዋል ሲል ኤን.ቢ.ሲ ኒውስ ዘግቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...