በኢትዮጵያ ከልጅነት ጋብቻ ጋር በተገናኘ ለህልፈት የሚዳረጉ በርካታ ሴት ህፃናት መኖራቸው ተገለፀ

Date:

በኢትዮጵያ እድሜያቸው ከ18 አመት በታች የሆኑ ሴት ህፃናት ከልጅነት ጋብቻ ጋር በተያያዘ ለህልፈት እንደሚዳረጉ የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

በሚኒስቴሩ የስነተዋልዶ ጤና ፣የቤተሰብ እቅድ፣የአፍላወጣቶችና ወጣቶች ፕሮግራም ሀላፊ ዶክተር አለማየሁ ሁንዱማ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት የስነተዋልዶ ጤናን ተደራሽ ለማድረግ የተለያዮ ስራዎች ተሰርተዋል።

ይህም የእናቶችን ሞት ለመቀነስ ጉልህ ሚና እንዳለው የተገለፀ ሲሆን አሁን ላይ ከልጅነት እርግዝና ጋር በተገናኘ በርካታ ሴት ህፃናት ለህልፈት እንደሚዳረጉ ተጠቅሷል።

በእዚህ የእድሜ ክልል ውስጥ እያሉ በጋብቻ በሚቆዮበት ወቅት ብዙ ቁጥር ያላቸውን ልጆች የመውለድ እድል ስላላቸው በወሊድ ጊዜ ለሞት ሊጋለጡ የሚችሉበት ሁኔታ መኖሩ ተገልጿል።

ይህም አዲስ አበባን እና ድሬደዋን ጨምሮ በሌሎች ስፍራዎች የሚታይ ነው ያሉት ሀላፊው በአርብቶ አደርና በከፊል አርብቶ አደር ቦታዎች ችግሩ በስፋት ይስተዋላል ብለዋል።

በኢትዮጵያ አሳሳቢ እየሆነ የመጣውን የልጅነት እርግዝናን ለመከላከል እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ የሚቆይ ፍኖተ ካርታ መዘጋጀቱን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...