የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከ59 ቢሊየን ብር በላይ እንደሚያስፈልገው ገለጸ

Date:

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተሻለ የትምህርት ተቋም ለመሆን በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ 59 ቢሊየን ብር እንደሚያስፈልገው የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝደንት ሳሙኤል ክፍሌ አስታወቁ።

ዩኒቨርሲቲው በአሁኑ ወቅት በዓመት ከአራት ቢሊየን ብር የመንግስት በጀት እንዲሁም ከአንድ ቢሊየን ብር የራሱ ገቢ ያገኛል።

ሆኖም ፕሬዝደንቱ ይህ በቂ እንዳልሆነና ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራቱን ለማሻሻል፣ ምርምሮችን ለማስፋፋትና ለተማሪዎች ምቹ የሆነ የትምህርት ከባቢ ለመፍጠር በዓመት ከ11 ቢሊየን ብር በላይ እንደሚያስፈልገው ተናግረዋል።

የገንዘብ እጥረት ዩኒቨርሲቲው እነዚህን ግቦች ለማሳካት በሚያደርገው ጥረት ላይ እንቅፋት እየሆነ መሆኑንም ፕሬዝደንት ሳሙኤል ክፍሌ ገልጸዋል።

ቅዳሜገበያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከምርጫው ራሳቸውን አገለሉ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮሚያ...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...