የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የብድር ጣሪያን ማንሳቱን አስታወቀ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ ከዚህ ቀደም በባንኮች ላይ ጥሎት የነበረውን ጊዜያዊ የብድር ጣሪያ ሙሉ በሙሉ ማንሳቱን ገልጿል። ይህ ውሳኔ ወደ ገበያ መር የገንዘብ ፖሊሲ ስርዓት ለመሸጋገር የተወሰደ እርምጃ መሆኑ ተጠቅሷል።

የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ባንኩ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔን በአንድ በመቶ ከፍ አድርጓል። በተጨማሪም የዋጋ ግሽበትን ለመከላከል የሚያስችል አዲስ የታለመ የመጠባበቂያ ግዴታ ማዕቀፍ አስተዋውቋል።

ከውጭ ንግድ ጋር በተያያዘም ባንኩ የውጭ ምንዛሪ ኮሚሽንን ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ ዝቅ አድርጓል። እንዲሁም ላኪዎች የሚያገኙትን የውጭ ምንዛሪ ለባንክ የመሸጥ ግዴታ (Surrender requirement) ከ50 በመቶ ወደ 30 በመቶ ዝቅ በማድረግ፣ የላኪዎችን ተወዳዳሪነት ለማሳደግና የውጭ ምንዛሪ ገበያውን ለማጠናከር አቅዷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...