የኢትዮጵያ የጨቅላ ህፃናት ህክምና ማኅበር ይፋዊ ምስረታውን አከበረ።

Date:

“ጤናማ ጅማሮ ለሁሉም ህፃናት” በሚል መርህ ዛሬ በሂልተን አዲስ አበባ ሆቴል ባካሄደው መርሃ ግብር ነው ምስረታውን ያከበረው።

​በጨቅላ ህፃናት ሰብ-ስፔሻሊስት ሐኪሞች የተመሰረተው የኢትዮጵያ የጨቅላ ህፃናት ህክምና ማኅበር በሀገሪቱ የጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስና የእንክብካቤ ጥራትን ማሻሻል ዓላማው እንዳደረገ ተገልጾአል።

በምስረታ በዓሉ ላይ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ “የኢትዮጵያ የጨቅላ ህፃናት ህክምና ማኅበር መመስረት የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ ለሚያደርገው አገራዊ ጥረት ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው።

መንግስት የጨቅላ ህፃናትን የህክምና አገልግሎት ተደራሽነት እና ጥራት ለማሻሻል የፖሊሲ እና የስትራቴጂ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።

ይህ ማኅበር በማስረጃ ላይ የተመሰረቱ የህክምና አሰራሮችን በመዘርጋት እና የባለሙያዎችን አቅም በመገንባት ረገድ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን እና ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በቅርበት እንደሚሰራ ሙሉ እምነት አለኝ።” ብለዋል።

የምስረታ ጉባኤው መሪ ቃል “ጤናማ ጅምር ለሁሉም ኢትዮጵያ ህፃናት” (Healthy Start Beginning for All Children Born Across Ethiopia) የሚል ነው።

​በኢትዮጵያ የጨቅላ ህፃናት ጤና ላይ ያሉ ተግዳሮቶች ​ኢትዮጵያ ባለፉት አመታት ከ5 አመት በታች ያሉ ህፃናትን ሞት በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ስኬት ያስመዘገበች ቢሆንም፣ የጨቅላ ህፃናት (ከተወለዱ ጀምሮ እስከ 28 ቀናት ባለው ጊዜ ውስጥ ያሉ) ሞት አሁንም ከፍተኛ ሀገራዊ ትኩረት የሚሻ ፈተና ሆኖ ቀጥሏል።

የቅርብ ጊዜ መረጃዎች እንደሚያሳዩት፦
​40% የሞት ድርሻ፦ በሀገሪቱ ከሚከሰቱት ከ5 አመት በታች ህፃናት ሞት ውስጥ ወደ 40% የሚጠጋው ድርሻ የጨቅላ ህፃናት ሞት ነው።

​ሊከላከሏቸው የሚችሉ መንስኤዎች፦ በየአመቱ በሺዎች የሚቆጠሩ ጨቅላ ህፃናት ሊከላከሏቸው እና ሊታከሙ በሚችሉ እንደ ያለዕድሜ መወለድ (Prematurity)፣ መታፈን (Birth Asphyxia) እና በኢንፌክሽን ምክንያት ህይወታቸውን ያጣሉ።

ይህ አሃዝ እንደሚያሳየው የማህበሩ መመስረት እና የባለሙያዎች ቅንጅት በሀገሪቱ የእንክብካቤ ጥራትን ለማሻሻል እና የዘላቂ ልማት ግቦችን (SDGs) ለማሳካት ወሳኝ ሚና ይጫወታል።

የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ​ዶ/ር አስራት ድምፀ በበኩላቸው “ማኅበራችን ‘ጤናማ ጅምር ለሁሉም ጨቅላ ህፃን’ በሚል መሪ ቃል የተመሰረተ ሲሆን፣ ዋነኛ ዓላማችን በኢትዮጵያ የሚወለድ እያንዳንዱ ጨቅላ ህፃን በወቅቱ የሚገኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ፍትሀዊ፣ በሳይንሳዊ ማስረጃ የተደገፈ፣ ከፍተኛ ጥራት ያለው እና ርህራሄ የተሞላበት የጨቅላ ህፃናት ህክምናና እንክብካቤ እንዲያገኝ ማስቻል ነው።

ዛሬ በይፋ ስራችንን ስንጀምር ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያካተተ ቅንጅታዊ አሰራር በመፍጠር የህፃናትን ሞት ለመቀነስ ቆርጠን ተነስተናል።” ሲሉ ገልጸዋል።

​የማኅበሩ 4ቱ ዋና ዋና ተልዕኮዎች
​የኢትዮጵያ የጨቅላ ህፃናት ህክምና ማኅበር በሀገሪቱ የህክምና ስርአት ውስጥ ዘላቂ ለውጥ ለማምጣት የሚከተሉትን አራት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ይዞ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

በተያያዘ ​የሙያዊ አቅም ግንባታ መፍጠር በጨቅላ ህፃናት ህክምና ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎችን አቅም በስልጠና እና በትምህርት ማሳደግ።

​በማስረጃ ላይ የተመሰረቱ አሰራሮችን መዘርጋት፦ በሳይንሳዊ ማስረጃዎችና ምርምሮች ላይ የተመሰረቱ የህክምና አሰራሮችን መዘርጋትና ማሻሻል።

​የፖሊሲ ለውጥ ማምጣት፦ ለጨቅላ ህፃናት ጤናና ደህንነት ምቹ የሆኑ ሀገራዊ የጤና ፖሊሲዎች እንዲቀረፁና እንዲሻሻሉ ተፅዕኖ መፍጠር Billboard፣ ​ቅስቀሳ እና ትብብር መፍጠር፦ የጨቅላ ህፃናትን ጤና በተመለከተ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ ማድረግ፤ እንዲሁም የጨቅላ ህፃናትን ሞት ለመቀነስ ሰፊ የህብረተሰብና የሙያተኞች ቅስቀሳ ማካሄድ።

ማኅበሩ ከህፃናት ስፔሻሊስት ሐኪሞች፣ ከጨቅላ ህፃናት ፌሎ ስፔሻሊስት ተማሪዎች፣ ከነርሶች እንዲሁም በጨቅላ ህፃናት ጤና ላይ ከሚሰሩ ማናቸውም የጤና ባለሙያዎች ጋር በመተባበር በሀገሪቱ የሚወለዱ ህፃናትን ህይወት ለመታደግ በትጋት እንደሚሰራ አስታውቋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የማኅበሩ አመራሮች፣ የጨቅላ ህፃናት ስፔሻሊስት ሐኪሞች፣ ነርሶች፣ ባለድርሻ አካላት እና ደጋፊ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች (NGOs) የተገኙ ሲሆን ማኅበሩ በሀገሪቱ የጨቅላ ህፃናትን የጤና ችግሮች በዘላቂነት ለመቅረፍ ከመንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች፣ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና ከሌሎች አለም አቀፍ የጤና ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት ሁልጊዜም በሩ ክፍት መሆኑን እያስታወሰ፣ ህብረተሰቡና የጤና ባለሙያዎች ለዚህ ቅዱስ አላማ መሳካት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ጥሪውን ያቀርባል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...