የእስራኤል እና ግብጽ ፍጥጫ

Date:


ግብፅ የፍልስጤም መንግስት እስካልተመሰረተ ድረስ ከእስራኤል ጋር የጠበቀ የዲፕሎማሲ ግንኙነት እንደማይኖር አስታወቀች፡፡

ካይሮ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንደተጠበቀ ሆኖ እንዲቀጥል ፍላጎት እንዳላት ግን ከመገልጽ አልተቆጠበችም፡፡

ግብጽ በህዝብ ደረጃ የሚደረግ መደበኛ ግንኙነት ሊኖር የሚችለው በፍልስጤም ሁሉን አቀፍ የሰላም ስምምነት ሲደረስ ብቻ መሆኑንም ይፈ አድርጋለች።

ምንም እንኳ ግብፅ እና እስራኤል ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ቢኖራቸውም፣ ህዝባዊ ትስስሩ የሚጸናው፤ የፍልስጤም ጉዳይ መፍትሄ ከማግኘቱ ጋር የተያያዘ መሆኑ ሀገራቱ ውዝግብ ውስጥ እንዲቆዩ አድርጓቸዋል።

ይህ የግብፅ አቋም፣ በቀጠናው እየተከሰቱ ያሉ የፖለቲካ ለውጦችን የሚያሳይ እና የሀገሪቱን የውጭ ፖሊሲ የሚያንፀባርቅ ነው ተብሏል።

ግብፅ የ1967ቱ የድንበር መካለልን ተከትሎ ሉዓላዊ የፍልስጤም መንግስት እንዲቋቋም ትፈልጋለች፡፡

ቲ አር ቲ እንደዘገበው፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች  565 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ አላሳለፉም

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና በተመዘገበው ውጤት...

የአማርኛ ቋንቋ እውነተኛ ምንጭ ቤተ መንግሥት ሳይሆን ሕዝብና ሠራዊት ነው

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአማርኛ ቋንቋ ማበልጸጊያ ተቋም አዘጋጅነት ከስድስት...

አዲስ አበባ፦ የዜጎች ቀይ መስመር!

(የግል አስተያየት) አዲስ አበባ የኢትዮጵያውያን መናገሻ፣ የበርካታ ብሔረሰቦች ባህሎች ለዘመናት...

አብን የምክክሩን ውጤት ውድቅ አደረገ!

አብን በሀገራዊ ምክክሩ ማጠቃለያ ላይ የተፈጸመውን “ሕገ-ወጥ ጣልቃ-ገብነት” በመቃወም...