የእቴጌ ጣይቱ እና ዳግማዊ ምኒልክ ታሪክን የሚዳስስ መጽሐፍ ተመረቀ

Date:

“እቴጌ ጣይቱ እና ዳግማዊ ምኒልክ፡ ኢትዮጵያ ከ1883-1910 [እ.ኤ.አ]” የተሰኘ የትርጉም መጽሐፍ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ተመረቀ።

መጽሐፉ የዓድዋን 130ኛ የድል በዓል እና 50ኛውን የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን መታሰቢያ በማድረግ ነው ለንባብ የበቃው።

የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ትናንት ቅዳሜ መጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም. የተከናወነ ሲሆን በመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ ምሁራንና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።

መጽሐፉ የተጻፈው በክሪስ ፕራውቲ ሲሆን በዶክተር መሠረት መንግሥቱ አሳታሚነት እና ተርጓሚነት፤ እንዲሁም በህይወት ተፈራ እና በዮርዳኖስ አልማዝ ሰይፉ ተርጓሚነት ተዘጋጅቷል።

የታሪክ ድርሳኑ እቴጌ ጣይቱ ብጡል በሀገር አመራርና በዓድዋ ድል የነበራቸውን ዲፕሎማሲያዊና ስትራቴጂካዊ ሚና እንዲሁም ዳግማዊ ምኒልክ ኢትዮጵያን ወደ ዘመናዊነት ለማሸጋገር ያከናወኗቸውን የተሃድሶ ሥራዎች በዝርዝር ይዳስሳል።

ከ1883 እስከ 1910 እ.ኤ.አ ባለው ጊዜ ውስጥ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት የጸናበት እና ዘመናዊ የመንግሥት መዋቅር የተዘረጋበት ወቅት እንደሆነ በመድረኩ ተገልጿል።

በጠቅላላው 457 ገጾች ያሉት መጽሐፉ በ1ሺህ ብር ዋጋ ለገበያ ቀርቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...