የዩክሬይን ወታደሮች በሱዳን

Date:

ጄኔራል አልብሩሀን በርካታ የዩክሬይን ቅጥረኛ ወታደሮችን “መደምሰሳቸውን” አስታወቁ፡፡

በሌተና ጄኔራል አብዱል ፈታህ አልብሩሀን የሚመራው የሱዳን ጦር ሀይል ባወጣው መግለጫ በዳርፉር ግዛት እየተካሄደ ባለው ጦርነት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የውጭ አገር ቅጥረኛ ወታደሮች መገደላቸውን ገለፀ፡፡

ከእነዚህ ውስጥ የዩክሬይን ወታደሮች እንደሚገኙበትም አስረድቷል፡፡

እንደመግለጫው የጦር ሀይሉ 6ተኛ ክፍለ ጦር በአልፈሽር ውስጥ በሚገኘው አል ካራማ የተሰኘ አደባባይ ላይ ባከናወነው ልዩ ዘመቻ የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አድርሷል፡፡

በዚህም ለፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ ተሰልፈው ሲዋጉ የነበሩ የውጭ አገር ወታደሮች የኪሳራው አካል መሆናቸውን አስታውቋል፡፡

እንደመግለጫው ከተገደሉት ውስጥ የዩክሬይንና የኮሎምቢያ ዜግነት ያላቸው ቅጥረኞች ይገኙበታል፡፡

በመግለጫው እነዚህ ቅጥረኛ ወታደሮች የድሮን ኦፐሬተርና የስናይፐር ተኳሽ በመሆን ሲሰሩ የነበሩ መሆናቸውንም አስረድቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...