የግብዓት ዋጋ እስከ 400 በመቶ በመጨመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች እንዲጓተቱ ምክንያት ሆኗል

Date:

የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር እንደገለፀው የግንባታ ግብዓቶች ዋጋ እስከ 400 በመቶ መጨመሩ የመንገድ ግንባታው የሚፈለገውን ደረጃ ላይ እንዳይደርስ ምክንያት ሆኗል።

ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ እንደተናገሩት ይህንን ችግር ለመቅረፍ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን በማቆም ነባሮችን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ሆኖም ቃል የተገቡ ሁሉም የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይጠናቀቁ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።

የምክር ቤት አባላትም ከ1980 ጀምሮ በጥናት የተለዩ መንገዶች እንዳልተገነቡ፣ የተጀመሩት በጊዜያቸው አለመጠናቀቃቸውንና የተሰሩትም ሳይገለገሉ መበላሸታቸውን አንስተዋል። በተጨማሪም ለመንገድ ልማት የተነሱ ዜጎች ለዓመታት ካሳ ሳይከፈላቸው መቆየታቸውንም ካፒታል ሰምቷል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን በበኩላቸው የመንገድ ግንባታ መጓተት የካሳ ክፍያና የግንባታ ግብዓት አቅርቦት ችግር መሆኑን አምነዋል። ችግሩን ለመፍታትም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...