የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

Date:

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት ብቻ 28 የደቡብ ሱዳን እና የሶማሊያ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር እየኖሩ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ማስተሳሰሩን አስታውቋል።

በመርሃ-ግብሩ ከ2012 እስከ 2018 ዓ.ም. ድረስ ለ7 ተከታታይ ዓመታት በተከናወኑ ስራዎች በርካታ ተማሪዎችን ከቤተሰቦች ጋር በማስተሳሰር ተማሪዎች ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው እንዲኖሩና እንዲማሩ እድል መፍጠሩን ተንግረዋል፡፡

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ታደሰ ወልደገብርኤል እንደገለጹት፤ መርሃ-ግብሩ ከኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በተጨማሪ ዓለም አቀፍ ተማሪዎችን ከቤተሰቦች ጋር አስተሳስሯል።

ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው የባዕድነት ስሜት እንዳይሰማቸው እና ተረጋግተው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ለማድረግ መርሃ-ግብሩ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ተገልጿል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ መርሃ-ግብሩን ለማስፋት ግልጽ የሆነ የአሰራር ስርዓት፣ የተወሰነ የስራ መዋቅር፣ በቂ በጀት እና የተቀናጀ የዩኒቨርሲቲና የከተማ አመራር ትብብር እንደሚያስፈልግ ኃላፊው አስገንዘብተዋል።

በሰላም ሚኒስቴር በኩል የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብን ተሞክሮ በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ለማስፋት ባለሙያዎችን በመመደብ እና ተቋማትን በመደገፍ ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸው ተመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ይህንዓለም አቅናው የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደጉ ከሚገኙ እና ከፍተኛ የባለአክስዮኖች ቁጥር ካላቸው...

ማዕቀቦች የኢራንን የኒውክሌር መርሃ-ግብር ቢያደናቅፉም መንግስቱን ሊጥሉ እንደማይችሉ ተገለጸ

ማዕቀቦች የኢራንን ወታደራዊ እና የኒውክሌር እንቅስቃሴዎች አስቸጋሪና ውድ እንዲሆኑ...

የአፍሪካ ሀገራት አዲስ የኢንቨስትመንት ፈንድ ይፋ አደረጉ

በአፍሪካ ሀገራት ላይ የተደቀነውን ከፍተኛ የብድር ጫና ለማቃለል እና...

ዶናልድ ትራምፕ “በቅርቡ” ሆርሙዝ የአሜሪካ ግዛት አካል እንደሚሆን ተናገሩ

ከኢራን ጋር ያለው ግጭት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካው...