“ግራ ቀኝ” ተከታታይ ድራማ ወደ ፊልም ሊቀየር ነው

Date:

“ግራ ቀኝ” ተከታታይ ሲትኮም ድራማ ወደ ፊልም ተቀይሮ ሊሠራ እንደኾነ ተጠቆመ። በሀማ ቱማ በእንግሊዝኛ ተጽፎ በሕይወት ታደሰ “የሶሻሊስቱ ጠንቋይ ነገር” በሚል ርዕስ ወደ አማርኛ የተተረጎ መጽሐፍን መነሻ በማድረግ የተዘጋጀው “ግራ ቀኝ” ተከታታይ ሲትኮም ድራማ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሲቀረብ ቆይቷል። “ግራ ቀኝ” በተከታታይ ሲትኮም ድራማ መልክም በሁለት ምዕራፎች እና በ24 ክፍሎች የቀረበ ሲኾን አበበ ባልቻ፣ ግሩም ዘነበ፣ ሚካኤል ታምሬ ከተጋባዥ ተዋናዮች ጋር በጋራ ተውነውበታል። መስከረም 29 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ራስ መኮንን አዳራሽ ውስጥ የድራማው የምዕራፎች ማጠቃለያ መርሐግብርም ተካሄዷል። በምዕራፎቹ የማጠቃለያ ዝግጅት ላይም “ግራ ቀኝ” ተከታታይ ሲትኮም ድራማ ወደ ዘጠና ደቂቃ የሚፈጅ ፊልም ተቀይሮ ለተመልካቾች እንደሚቀርብ የድራማው አዘጋጅ ድርብድል አሰፋ ተናግሯል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...