ጤና ሚኒስቴር አንድ ተጨማሪ ሰው በማርበርግ ቫይረስ በሽታ መያዙን አስታወቀ

Date:

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል #ጂንካ ከተማ በተከሰተው ማርበርግ ቫይረስ አንድ ተጨማሪ ሰው መያዙን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴሩ፣ ትላንት ህዳር 9 ቀን 2018 ዓ.ም. ዘጠኝ የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ አንድ ሰው በቫይረሱ መያዙን ማረጋገጡን ገልጿል።

በዚህም አጠቃላይ በማርበርግ ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 4 ደርሷል ብሏል። የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ የቫይረሱ ምልክት ታይቶባቸው ህይወታቸው ካለፈ ስድስት ሰዎች መካከል ሦስቱ ሰዎች የሞቱት በቫይረሱ መሆኑን ህዳር 8 ቀን በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል።

ይህ በእንዲህ እያለ የማርበርግ ቫይረስ በሽታን በመከላከል እና በመቆጣጠር ረገድ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ የ #አሜሪካ መንግስት ዝግጁ መሆኑን አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ገልጸዋል።

አምባሳደሩ ይህን የገለጹት፣ በኢትዮጵያ በተከሰተው የማርበርግ የቫይረስ በሽታ አጠቃላይ እና ፈጣን ምላሽ መስጠት ዙሪያ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ጋር ትላንት በተወያዩበት ወቅት ነው።

ዶ/ር መቅደስ የበሽታውን የላብራቶሪ ምርመራ፣ ከታማሚዎች ጋር የነበሩ ንክኪዎች ክትትል፣ የአደጋ ዝግጁነት እና የማህበረሰብ ተሳትፎን ጨምሮ አስቀድመው የተተገበሩ ዘርፈ ብዙ እርምጃዎችን አብራርተዋል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...