ሀርቫርድ ዩኒቨርስቲ ዓለም አቀፍ ተማሪዎችን እንዳይቀበል ተከለከለ

Date:

የትራምፕ አስተዳደር ሀርቫርድ ዩኒቨርስቲ ዓለም አቀፍ ተማሪዎችን እንዳይቀበል ያገደ ሲሆን ይህም ከአሜሪካ አንጋፋው ዩኒቨርስቲ ጋር ያለውን አለመግባባት አባብሶታል።

የአገር ውስጥ ደህንነት መስርያ ቤት ኃላፊ ክሪስቲ ኖኤም በኤክስ ገጻቸው ላይ እንደጻፉት አስተዳደሩ ሀርቫርድ “ተማሪዎች እና ስደተኛ ያልሆኑ ተማሪዎችን መቀበል የሚያስችለውን ዕድል ሕግን ማክበር ባለመቻሉ ምክንያት ተሰርዟል” ብለዋል።

“ይህ በመላው አገሪቱ ለሚገኙ ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች እና የትምህርት ተቋማት እንደ ማስጠንቀቅያ ይሁናቸው” ሲሉ ሐሙስ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ልጥፍ ላይ ጽፈዋል።

ሀርቫርድ ውሳኔውን “ሕገ ወጥ” ሲል በመግለጫው አውግዞታል።

“ከ140 በላይ አገራት የመጡ እና ዩኒቨርሲቲውን እና ይህችን አገር በማይተመን መልኩ የሚያበለጽጉትን ዓለም አቀፍ ተማሪዎቻችንን እና ምሁራኖቻችንን ለማስተናገድ ሙሉ በሙሉ ቁርጠኞች ነን” ሲል ዩኒቨርሲቲው በመግለጫው ላይ ምላሽ ሰጥቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...