” ህብረተሰባችን፣ ሰፊው የንግድ ማህበረሰብም የተቀመጠለት መፍትሄ የለም ” – ማህበሩ

Date:



ከዛሬ ጀምሮ እቃን በፌስታል ይዞ መንቀሳቀስ ያስቀጣል።

የፕላስቲክ ኢንዱስትሪው ከስራው እንዲወጣ መደረጉ በ100 ሺሕዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞችንና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተጠቃሚዎችን የሚጎዳ በመሆኑ “በድጋሚ እንዲጤን” የኢትዮጵያ ፕላስቲክ እና ጎማ አምራቾች ማህበር አሳስቧል።

የማህበሩ አባል እና ጉዳዩን በሚደነግገው አዋጅ ምክንያት የተቋቋመው ኮሚቴ ጊዚያዊ ሰብሳቢ አቶ በረከት ገ/ህይወት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ ” አሁንም ቆም ተብሎ ቢታሰብበት መልካም ነው ” ብለዋል።

አቶ በረከት በዝርዝር ምን አስተያየት ሰጡ ?

” የሚፈጠረውን አብረን እናያለን። ከዚህ በፊት በአጽንኦት ያሳሰብናቸው መሰረታዊ ጉዳዮች አሉ፤ የተኪ ምርቶች ሁኔታ በአግባቡ አልታየም።

ኢንዱስትሪዎች በቂ የሽግግር ጊዜ ያስፈልጋቸዋል። ካልሆነ ይከስማሉ፣ ሠራተኞች ይበተናሉ፤ ለሀገርም የምናበረክተው አስተዋጽኦ በዜሮ ይባዛል። ህብረተሰባችን ምቹና ተመጣጣኝ የሆነ ሸቀጦችን የሚሰበስብበት ግብዓትን እንዲያጣ ይደረጋል፤ በዚህ ምክንያት ላላስፈላጊ የኑሮ ውድነትም ይጋለጣል።

ተኪ የሚባል ነገር ቢገኝ እንኳ (አሁን ባለው ሁኔታ እሱን የሚያሳይ ነገር ባይኖርም) በዋጋ፣ በቅልጥፍና፣ በምቾት፣ ሁሉንም አይነት እቃ ለመያዣነት የማገልገል ባህሪ ስለሌላቸው ሌሎች ማሸጊያዎች ህብረሰተባችን፣ ሰፊው የንግድ ማህበረሰብም የተቀመጠለት መፍትሄ የለም። ዓይን ጨፍኖ እየተገባበት ነው ያለው።

ይመጣሉ ካልናቸው ችግሮች የደረሱ አሉ። ወደ ፊት የሚያጋጥሙትን አብረን የምናያቸው ይሆናል። ስለዚህ አሁንም ቆም ተብሎ ቢታሰብበት መልካም ነው ” ብለዋል።

ቲክቪህ ኢትዮጵያም፣ ተተኪ ምርቶች እንደሚመረቱ በመንግስት በኩል ተገልጿል፤ ለዚህም ” ጊዜም ተሰጥቷል” ተብሏል። ተተኪ ምርቶቹን ለማምረት የምትችሉበት ሁኔታ አለ ? ሲል አቶ በረከትን ጠይቋል።

ምን መለሱ ?

” የለም። ፈጽሞ ሊሆን እንደማይችል እኮ ተነጋግረናል። የፕላስቲክ ከረጢት ማምረቻ ኢንዱስትሪዎች እነርሱ የሚሏቸውን ሌላ ተኪ ምርቶች ሊያመርቱበት የሚችል ቴኪኒክ በፍጹም የለም፤ ያ ሊሆን አይችልም ማለቴ ነው።

ስለዚህ ሌላ ኢንዲስትሪ ነው የሚቋቋመው ይሄንን ወደዛ Shift ማድረግ አይቻልም። ቴክኒካሊ የተዘጋ ዜሮ ነገር ነው። በዛ ላይ ኢንዱስትሪዎች ድጋፍ ተሰጥቷቸው ወደዛ ገብተዋል የሚባለው ምንም መሰረት፣ ሐቅ የሌለው ነው።

በማህበራችን የተጠለሉ በርካታ አምራቾች አይደለም አንድ በነጠላ ደረጃ ወደሌላ ኢንዲስትሪ የተሸጋገረ የለም። ወደ ኢንዱስትሪ የሚገባው ደግሞ በ6 ወራት ውስጥ አይደለም። ወደ ሌላ ኢንዱስትሪ ለመግባት ጥናት፣ Supplayer መለየት፣ ማሽን መምረጥ ያስፈልጋል። ለዚህ የማያስፈልግ Resource Allocate ማድረግንም ይጠይቃል።

አብዛኛው ከውጭ የሚመጣ ቴክኖሎጂ ስለሆነ፣ የጉምሩክ እና ሌሎች አጠቃላይ ስራዎች ሲደመሩ በ6 ወራት የሚጠናቀቅ ስራ አይደለም። ጊዜ የሚፈልግ ነገር ነው። ከIndustrialization ወደ ጋርዮሽ System እንግባ ካልን ዓይናችንን ጨፍነን መግባት እንችላለን።

ሰዎች በእጃቸው ወረቀትን እያጣበቁ በቀን ውስጥ ሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ግብይቶች መፍትሄ ያቀርባሉ ማለት አይቻልም። አሁን ባለው ሁኔታ ወረቀት እንኳን ለማሸጊያነት አይደለም ለኀትመት ውድ ከመሆኑ የተነሳ መፅሐፍትና ጋዜጦች መታተም እንዳቆሙ መናገር ለቀባሪ ማርዳት ነው።

አሁን ባለው ሁኔታ ወረቀት እጅግ ውድ ነው። እንኳን ሙዝ፣ ብርቱካን በርበሬ እና ቃሪያ ሊያዝበት ደራሲያን መፅሐፍ ማሳተሚያ ያቃታቸው አንዱ ችግር የወረቀት ውድነት በዋጋው ያሳደረው ተፅዕኖ ነው።

ጋዜጦችንና መፅሔቶችን ከገበያ ያወጣቸው ነው እንግዲህ ለማሸጊያ መፍትሄ ይሆናል የተባለው። እሱም በኢንዱስትሪ ደረጃ ሳይሆን በጎጆ ኢንዱስትሪ ሰዎች እጅ በእጅ እያጣፉ በሚያዘጋጁት ነው። ይሄ በጣም የሚያሳዝን ነው እንደ ፓሊሲ አማራጭ መቅረቡ።

በተጨማሪ ደግሞ ‘ቃጫ፣ ኮባ’ እየተባለ (ለእቃ መያዣነት) የሚጠቀሰውን እኔ ስላቅ ነው የምለው።

አንድ ተቋም አንድን ነገር በሌላ መልክ ይተካ ሲል በትክክል ጥናት ተደርጎ፣ በብቃት፣ በምቾት ሌላ ነገር እንዴት ይተካዋል ይባላል? እንጁ ኢንዱስትሪን በጋርዮሽ ሲስተም መተካት ዘመኑን ያልዋጀ መፍትሄ ስለሆነ ማህበራችን፣ አምራችን ያሳዘነ፣ ህብረተሰባችንን ለከፍተኛ እንግልት የሚዳርግ መሆኑን ቀድመን አሳስበናል፤ ቀድሞ የተወሰደ መፍትሄ ባይኖርም። አሁንም አልረፈደም ነገሮችን ለማስተካከል።

ኢኮኖሚው ሳይጎዳ፣ ሠራተኞች ሳይበተኑ ህብረተሰቡ ምቹ የማሸጊያ አማራጮች ሊቀርቡለት ሲገባ ግለሰብ ቤት ለመቀየር አንድ አመት ይሰጠው በሚባልበት ዘመን ከአንድ ኢንዱስትሪ ወደ ሌላ ለመሸጋገር 6 ወር በቂ ነው፤ ለዚህም የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ አይተናል ተብሎ።

Micro የሆኑ አገሮችን (በኢትዮጵያ Context ከአንድ ክፍለ ከተማ በላይ ህዝብና ኢኮኖሚ የሌላቸውን አገሮች ለኢትዮጵያ ምሳሌ አቅርቦ) እንደዚህ ነው የተደረገው ብሎ ማለት የሚያመጣውን የጉዳት መዘዝን አብረው የምናየው ይሆናል ” ብለዋል።

በአጠቃላይ ስንት ሠራኞች አሉ ? ለሚለው ጥያቄም፣ ” በፕላስቲክ ኢንዱስትሪው ከ100 ሺሕ በላይ ሠራተኞች በቀጥታ ቅጥር፤ በምርት ግብዓት ሰንሰለት እና ምርትን ከተመረተ በኋላ በግብይት ሰንሰለት ውስጥ አጠቃላይ ባሉ የፕላስቲክ ከረጢት ኢንዱስትሪው ከሚሊዮን ሰዎች ህይወት ጋር የተቆራኘ ኢንዱስትሪ መሆኑን አጥኚ ቡድኖች በጥናታቸው ያረጋገጡት ነው ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

” ስለዚህ የዚህ ሁሉ ህብረተሰብ የእንጀራ ገመድ ነው የሚበጠሰው” ብለው፣ “አሁን ባለው ኑሮ ውድነት ላይ ሌላ ኑሮ ውድነትን የሚያባብስ፤ ዜጎች ሥራ ሳይፈጠርላቸው በራሳቸው ጥረት አካባቢ ላይ ውድቆዳቂ ቆሻሻዎችን በመሰብሰብ፣ ለፋብሪካዎች ግብዓት በማቅረብ፣ አካባቢን ከብክለት እየታደጉ ለራሳቸው ለልጆቻቸውም እንጀራ የፈጠሩበትን ይሄንን ኢንዱስትሪ ከስራ እንዲወጣ የማድረግን ፍርድ ለታሪክ ትተነዋል ” ነው ያሉት።

@tikvahethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ አዲስ አበባ ገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ...

የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የ5 በመቶ የአደጋ ሥጋት ምላሽ ፈንድ ክፍያን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ

በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱት ሁለቱም የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ማለትም ኢትዮ ቴሌኮም እና...

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዚዳንት ለኢራን ህዝብ – “እኛ ከእናንተ ጋር ነን”

የአውሮፓ ፓርላማ ፕሬዝዳንት ሮቤርታ ሜትሶላ፥ የኢራን መንግስት በተቃዋሚዎች ላይ...

አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ሊኖራት ይገባል

በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አፍሪካ ቋሚ ውክልና...