
በዩናይትድ ኪንግደም የሚገኘው የህግ ባለሙያዎች ቡድን ለእስራኤል ወግነው በጋዛ ጦርነት ላይ በተሳተፉ 10 የእንግሊዝ ዜጎች ላይ የጦር ወንጀል ክስ ለማቅረብ ማቀዱን ዘ ጋርዲያን ዘግቧል። ቅሬታው ብሪታንያውያንን “በሲቪል አካባቢዎች ላይ ያለ አድሎአዊ ጥቃቶች” እና “በተከለከሉ ቦታዎች ላይ ታሪካዊ ሀውልቶችን እና ሃይማኖታዊ ቦታዎችን ጨምሮ በተጠበቁ ቦታዎች ላይ የተቀናጁ ጥቃቶች” ጋር እጃቸው አለበት ሲል ክስ መመስረቱን ይፋ አድርጓል።
በጉዳዩ ላይ ከተሳተፉት ጠበቆች መካከል አንዱ የሆኑት ታዋቂው ጠበቃ ሚካኤል ማንስፊልድ “የብሪታንያ ዜጎች በፍልስጤም ውስጥ ከተፈጸሙ ወንጀሎች ጋር እንዳይተባበሩ ህጋዊ ግዴታ አለባቸው፤ ማንም ከህግ በላይ አይደለም” ብለዋል። ማንስፊልድ የጠቀሰው የዘ ጋርዲያን ዘገባ ከሆነ “ከእኛ ዜጎቻችን አንዱ ጥፋት እየፈፀመ ከሆነ በዚህ ጉዳይ ላይ አንድ ነገር ማድረግ አለብን” ማለታቸውን አስነብቧል። “የውጭ ሀገራት መንግስታትን መጥፎ ባህሪን ማስቆም ባንችል እንኳን ቢያንስ በዜጎቻችን የሚፈፀሙ መጥፎ ባህሪን ልናቆም እንችላለን” ሲሉ አክለዋል።
በሌላ በኩል እስራኤል በጋዛ ሰርጥ ባለፉት 24 ሰዓታት በፈፀመችው ጥቃት ቢያንስ 57 ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች 137 ሰዎች ቆስለዋል ሲል የጋዛ የመንግስት ሚዲያ ጽህፈት ቤት ባወጣው ዘገባ አስታውቋል። እ.ኤ.አ. መጋቢት 18 ቀን እስራኤል በጋዛ ላይ ዳግም ጥቃቷን ከቀጠለች በኋላ የሟቾች ቁጥር 1,391 ሲደርስ 3,434 ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል። ከጥቅምት 7 ቀን 2023 ጀምሮ ያለው አጠቃላይ የተገደሉ ሰዎች ቁጥር አሁን ላይ 50,752 ሲደርስ 115 ሺ 475 ያህል ሰዎች ቆስለዋል።
@ዳጉ