ለ472 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ተደረገ!

Date:

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለ472 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ። የክልሉ መንግሥት ከፊታችን የሚከበረውን 1 ሺህ 446ኛውን የዒድ አልፈጥር በዓል እና መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ለ472 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉ ተገልጿል።

በወንጀል ጉዳይ እስራት ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤት ከሚገኙት ውስጥ ሕጉ የሚጠይቀውን መመዘኛ አሟልተው ለተገኙ በመደበኛ ለ459 ወንዶች እና ለ12 ሴቶች እንዲሁም በልዩ ሁኔታ ለ1 ሴት የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ ስለመደረጉ የክልሉ ርዕሰ መሥተዳደር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) መናገራቸውን የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል።

ይቅርታ ከተደረገላቸው ታራሚዎች መካከል፤ 471 በሙሉ ይቅርታ ከእስር እንዲለቀቁ መወሰኑም ተመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...