የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

Date:

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ በኩል የባንክ አገልግሎቶችን / Agency Banking ለመስጠት የሚያስችለውን ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ።

አሰራሩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የንግድ ባንኮች በጋራ በባለቤትነት የሚያስተዳድሩትን “ኢቲ-ስዊች” የክፍያ መረብ መሠረት ያደረገ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በ700 ቅርንጫፎች በሙከራ ደረጃ ሥራ መጀመሩና በወር ጊዜ ውስጥ በሙሉ አቅም በሀገር አቀፍ ደረጃ ሥራ እንደሚጀምር ተገልጿል።

በዚህም ደንበኞች የትኛውም የባንክ ሂሳብ ቢኖራቸው በፖስታ ቤት መስኮቶች በኩል ገንዘብ ገቢና ወጪ ማድረግ፣ የፍጆታ ክፍያዎችን መፈጸም እና የባንክ ሂሳባቸውን ማንቀሳቀስ ያስችላቸዋል።

በሌላ በኩል፣ ባንኮች ወጪ ለመቀነስ ሲሉ ቅርንጫፎቻቸውን በሚዘጉበት ወቅት የኢትዮ ፖስት ወደ አገልግሎቱ መግባት የተለያዩ አስተያየቶች እንዲነሱ አድርጓል።

አንዳንዶች የባንክ አገልግሎት ወደ ተንቀሳቃሽ ሞባይል በሰፊው እየተቀየረ ባለበት ወቅት ቅርንጫፎችን መሠረት ያደረገ አሰራር ውጤታማነቱ አጠራጣሪ እንደሆነ ሲገልጹ፤ ሌሎች ደግሞ አሰራሩ ባንኮች ባነሰ ወጪ ተዳራሽነታቸውን እንዲያሰፉ ይረዳል ሲሉ ያነሳሉ።

አዲስ ፎርቹን

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

«ግብጽ ዛቻውን አቁማ ወደ ድርድር ትግባ!»

ታዋቂው የአፍሪካ ፖለቲካ ተንታኝ ዶ/ር ዴቪድ ማትሳንጋ ግብጽ በኢትዮጵያ...

በብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ከ710 ሚሊዮን ዶላር በላይ ፍላጎት የቀረበበት መሆኑ ተገለጸ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባካሄደው የ500 ሚሊዮን ዶላር ልዩ የውጭ...