ሕብረት ባንክ 35 ሚሊየን ብር  ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች አበረከተ

Date:

35 ሚሊዮን ብሩ የተሰጠው ለ10  የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ነው፡፡ድጋፍ የተርገላቸው አስሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች የተመረጡት በሸሪዓው መርህ መሰረት የሚሰሩ መሆናቸው ተመዝኖ፣ ከሚደርሱት የሕብረተሰብ ቁጥር እና የሚሰጠውን ድጋፍ ለምን ተግባር እንደሚያውሉትም ጭምር ታይቶ ነው ተብሏል።

ድጋፉ ከተደረገላቸው ድርጅቶች መካከል፤ እማሙ ማሊክ ትምህርት ቤት፣ ወንድም ካሊድ ፋውንዴሽ፣ ባቡል ካኸር፣ ሜቄዶኒያ፣ ቢላሉ ሀበሺ እንዲሁም የኢትዮጵያ ሙስሊም የጤና ባለሞያዎች ማህበር ይገኙበታል።

ሕብረት ባንክ የሸሪዓውን መርህ በተከተለ መልኩ ከወለድ ነፃ የባንክ እገልግሎት መስጠት ከጀመረ 10 ዓመታት እንዳለፈው አስታውሷል።

በአሁኑ ሰዓትም ሕብረት ባንክ 23 ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ብቻ የሚሰጡ ቅርንጫፎች ከፍቼ እየሰራሁ ነው ሲል  ጠቅሷል።

ባንኩ ሸሪዓው በሚያዘውና የሕብረት ባንክም እንዱ እሴት የሆነውን የመረዳዳት ወይም ማሀበራዊ ሃላፊነትን የመወጣት ተግባር ለመከወን  ሕብረት ከሚሰጠው የባንክ አገልግሎች በሻገር በማሕበረሰቡ ሕይወት ውስጥ በጎ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ  ማሕበራዊ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚሰሩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን ሲደግፍ መቆየቱን አስታውሷል።

ትናንት ምሽት በሸራተን ሆቴል በተካሄደው ድጋፍ መስጠት ዝግጅት ላይ የሴቶችና የማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሁሪያ አሊ፣ ሌሎች የመንግስት ሹመኞች እንዲሁም የባንኩ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

ሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...