ሕወሓት ፌደራል መንግሥቱን ከሰሰ

Date:

ሕወሓት፣ የትግራይ ሕዝብ ፍትሃዊ ጥያቄ በጦርነት ዛቻ ሊታፈን አይችልም ሲል ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አቋሙን ገልጧል።

ከመሃል አገር ከሄደ የኃይማኖት ልዑካን ቡድን ጋር ሰሞኑን መወያየቱን የገለጠው ሕወሓት፣ የልዑካኑ አባላት በትግራይ ያለው “የሰላም ፍላጎት” እና “ዝግጁነት” ቀደም ሲል ከሠሙት የተለየ መኾኑን ተናግረዋል ብሏል።

ሕወሓት፣ በትግራይ በኩል ለግጭት የሚጋብዝ እንቅስቃሴ በሌለበት ኹኔታ ፌደራል መንግሥቱ የማስፈራራት ዘመቻ እያካሄደ፣ የታጠቁ ሃይሎችን እያደራጀና እያስታጠቀ ይገኛል በማለትም መክሰሱን ዋዜማ ዘግባለች፡፡

መንግሥት በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት ግዴታውን እስካልተወጣ ድረስ፣ የትግራይ ሕዝብ ከመሪ ድርጅቱ ጋር ለኅልውናውና ሉዓላዊነቱ ሠላማዊ የፖለቲካ ትግሉን ይቀጥላል ሲል ሕወሓት አቋሙን ገልጧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...