የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ከፉልሀም ጋር የፕርሚየር ሊግ መርሐግብር 2ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
የመድፈኞቹን የማሸነፊያ ግቦች ቡካዩ ሳካ እና ሚኬል ሜሪኖ ሲያስቆጥሩ ለፉልሀም ሙኒዝ ከመረብ አሳርፏል።
በጉዳት ለወራት ከሜዳ ርቆ የቆየው ቡካዩ ሳካ ወደ ሜዳ በተመለሰበት ጨዋታ ግብ ማስቆጠር ችሏል።
አርሰናል ማሸነፉን ተከትሎ ከሊጉ መሪ ሊቨርፑል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ዘጠኝ ማጥበብ ችሏል።
በሌላ ጨዋታ ዎልቭስ ከዌስትሀም ዩናይትድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?
2️⃣ አርሰናል :- 61 ነጥብ
8️⃣ ፉልሀም :- 45 ነጥብ
ቀጣይ መርሐግብር ?
ቅዳሜ – ኤቨርተን ከ አርሰናል
እሁድ – ፉልሀም ከ ሊቨርፑል
@tikvahethsport
