በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ሩብ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ አርሰናል ከሪያል ማድሪድ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2ለ1 ማሸነፍ ችለዋል።
የመድፈኞቹን የማሸነፊያ ግቦች ቡካዩ ሳካ እና ጋብሬል ማርቲኔሊ ሲያስቆጥሩ ለሪያል ማድሪድ ቪንሰስ ጁኒየር ከመረብ አሳርፏል።
አርሰናል ሪያል ማድሪድን በድምር ውጤት 5ለ1 በማሸነፍ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅለዋል።
ቶማስ ፓርቴ ቢጫ ካርድ መመልከቱን ተከትሎ የመጀመሪያው ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ በቅጣት ያመልጠዋል።
አርሰናል ከሪያል ማድሪድ ጋር ያደረጋቸውን አራት የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች አልተሸነፈም ሶስቱን ማሸነፍ ችሏል።
አርሰናል በግማሽ ፍፃሜው የፈረንሳዩን ሻምፒዮን ክለብ ፒኤስጂ የሚገጥሙ ይሆናል።
