ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ አዲስ ዘመናዊ አውሮፕላን ተረከበ

Date:


ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ3.6 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የገዛትን አዲስ ዘመናዊ አውሮፕላን በዛሬው ዕለት በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተረክቧል፡፡

አውሮፕላኗ 14 ሰው የመያዝ አቅም ያላት ሲሆን የተደራጀ የአውሮፕላን ማረፊያ በሌለባቸው ገጠራማ አከባቢዎች በቀላሉ ማረፍ እንደምትችልም ፤ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እህት ኩባንያ የሆነው ትራንስ ኔሽንስ ኤር ዌይስ ሥራ አስኪያጅ አቶ አሚር አብዱልወሃብ ለኢቢሲ ዶትስትሪም ተናግረዋል፡፡

“ሴስና ካራቫን ኤክስ” የሚል ስያሜ ያላት አዲሷ አውሮፕላን ሚድሮክ በማዕድን እና በእርሻ ዘርፍ የሚሰራቸው ሥራዎችን ለማሳለጥ ተጨማሪ አቅም እንደምትፈጥርም ጠቁመዋል፡፡

በተጨማሪም አውሮፕላኗ በኮንትራት ለጎብኚዎች እና ለአገልግሎት ፈላጊዎች የቻርተር አገልግሎት እንደምትስጥም አመላክተዋል፡፡

አውሮፕላኗ በአሜሪካው የአውሮፕላን አምራች ድርጅት ቴክስትሮን አቪዬሽን (Textron Aviation) ኩባንያ መሰራቷንም አመላክተዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የክሪፕቶ ሥራ ፈጣሪው የ15 ዓመት እስር ተፈረደበት

የቀድሞው የክሪፕቶከረንሲ ሥራ ፈጣሪ ተሰውሯል ከተባለ 40 ቢሊየን ዶላር...

5ኛው የኢሰመኮ ዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ፊልም ፌስቲቫል ተካሄደ

በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አዘጋጅነት በየዓመቱ በፈረንጆቹ ታኅሣሥ...

የንግድ ሚኒስቴር 13 ምርቶችን በመነሻ ሀገር የጥራት ማረጋገጫ (PVoC) እንዲያገኙ ወሰነ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት፣ በሀገር...

ገዳ ባንክ ከ444 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለፀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፤ ባንኮች የተከፈለ ካፒታላቸውን በ2018 ዓ.ም...