ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ አዲስ ዘመናዊ አውሮፕላን ተረከበ

Date:


ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ3.6 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የገዛትን አዲስ ዘመናዊ አውሮፕላን በዛሬው ዕለት በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተረክቧል፡፡

አውሮፕላኗ 14 ሰው የመያዝ አቅም ያላት ሲሆን የተደራጀ የአውሮፕላን ማረፊያ በሌለባቸው ገጠራማ አከባቢዎች በቀላሉ ማረፍ እንደምትችልም ፤ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ እህት ኩባንያ የሆነው ትራንስ ኔሽንስ ኤር ዌይስ ሥራ አስኪያጅ አቶ አሚር አብዱልወሃብ ለኢቢሲ ዶትስትሪም ተናግረዋል፡፡

“ሴስና ካራቫን ኤክስ” የሚል ስያሜ ያላት አዲሷ አውሮፕላን ሚድሮክ በማዕድን እና በእርሻ ዘርፍ የሚሰራቸው ሥራዎችን ለማሳለጥ ተጨማሪ አቅም እንደምትፈጥርም ጠቁመዋል፡፡

በተጨማሪም አውሮፕላኗ በኮንትራት ለጎብኚዎች እና ለአገልግሎት ፈላጊዎች የቻርተር አገልግሎት እንደምትስጥም አመላክተዋል፡፡

አውሮፕላኗ በአሜሪካው የአውሮፕላን አምራች ድርጅት ቴክስትሮን አቪዬሽን (Textron Aviation) ኩባንያ መሰራቷንም አመላክተዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በጤና አገልግሎት ማስታወቂያዎች ላይ የሕመምተኞችን ምስክርነት መጠቀም ተከለከለ

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት በኢትዮጵያ ውስጥ...

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...