ዶናልድ ትራምፕ ለቢቢሲ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፤ ከፑቲን ጋር የነበራቸዉ ልዩ የስልክ ለዉዉጥ ተስፋ ቢስ ቢሆንም ጉዳዩን ግን አልጨረስኩም ብለዋል፡፡
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት የሩሲያውን መሪ እንደሚያምኗቸዉ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽም፤ ማንም ሰው አላምንም ማለት ይቻላል ብለዋል፡፡
ትራምፕ ይህን የተናገሩት ለዩክሬን የጦር መሳሪያ ለመላክ ማቀዳቸውን ካስታወቁ ከሰዓታት በኋላ ሲሆን፤ በ50 ቀናት ውስጥ የእርቅ ስምምነት ካልተደረሰ በሩሲያ ላይ ከባድ ታሪፎች እንደሚጣሉ አስጠንቅቀዋል።
ትራምፕ በዩክሬን ጦርነትን ለማቆም ከሩሲያ ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ ለአራት ጊዜ ያህል አስበው እንደነበር ተናግረዋል።
ስለ ፑቲን ተጠይቀዉ በሰጡት ምላሽም ‹‹በእርሱ ተስፋ ብቆርጥም አልጨረስኩም፤ በእርሱ ግን ተስፋ ቆርጫለሁ›› ሲሉ መልሰዋል፡፡
‹‹ጥሩ ውይይት እናደርጋለን፤ ሂደቱም ጥሩ ነው ብዬ ሊሳካ እንደምንቃረብ ሳስብ እሱ በኪቭ አንድ ሕንፃ ያፈርሳል›› ብለዋል።
ማንም ሰው አላምንም ማለት ይቻላል- ትራምፕ
Date:
