ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምሁር ችግር ፈቺና መፍትሄ አሳሽ ነው አሉ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪ የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዩኒቨርሲቲው 75ኛ ዓመት የምሥረታ በዓልን ምክንያት በማድረግ “የምሁራን ሚና ለሀገራዊ ብልጽግና” በሚል ርዕስ የጥናታዊ ጽሁፍ አቅርበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ምሁር በስሜታዊነት የሚነዳ ሰው አይደለም ብለዋል።
ሐሳብ አክባሪ እና አፍቃሪ፤ ጥልቅ አሰላሳይ እና ብዙ ጠያቂ፤ አንባቢ፣ ነቃሽና ተንታኝነት የምሁር መገለጫዎች እንደሆኑ አስገንዝበዋል።
እንዲሁም ችግር ፈቺና መፍትሄ አሳሽነት የምሁር መገለጫ መሆኑን በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል።
