ሩሲያ እና ዩክሬን በኢስታንቡል ለድርድር መቀመጣቸው ለዓለም ሰላም መልካም ተስፋ ነው

Date:

ድርድሩ ጥሩ የሰላም ጅምር ነው ሲሉ በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ኢኒስቲትዩት የጥናትና ምርምር መሪ የሆኑት ዳርእስከዳር ታዬ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። አክለውም ዘላቂ ሰላም የግጭቱን ዋና መንስዔዎች መፍታት እንደሚሻ ጠቁመዋል።

🗣 “ለሩሲያውያን የግጭቱ ዋና መንስዔ የኔቶ ወደ ምስራቅ አውሮፓ መስፋፋት ነው። ሌላው ደግሞ ዩክሬን ሩሲያኛ ተናጋሪዎች ላይ የምታደርሰው በደል ነው” ብለዋል።

ተመራማሪው አውሮፓውያን ግጭቱ እየሄደ ባለበት መንገድ ደስተኛ እንዳልሆኑ፣ ዩክሬን እንድታሸንፍ እና ሩሲያን ድል ማድረግ እንደሚፈልጉ ገልፀው፤ ይህ የማይሆን ነው ብለዋል።

በአውሮፓውያን እና በአሜሪካውያን መካከል የተፈጠረው ወቅታዊ ልዩነት አሜሪካ ሰላምን እንድትመርጥ፤ አውሮፓ ግን ግጭቱ ይቀጥል የሚል አቋም እንድትይዝ ያደረገ ይመስላልም ብለዋል።

ይህ ክፍፍል መቀጠሉ ላይ ጥሪጣሪያቸውን የገለፁት ተመራማሪው፤ አውሮፓውያን ተቀበሉትም አልተቀበሉትም ሩሲያ እና ዩክሬን ስምምነት ላይ ይደርሳሉ ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...