የመኾኒ ከተማ ነዋሪዎች  በህወሓት ላይ የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

Date:

በመቶዎች የሚቆጠሩ የደቡብ ትግራይ መኾኒ ከተማ ነዋሪዎች፣ ዛሬ በሕወሓት ላይ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸውን የክልሉ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ነዋሪዎቹ ሰልፍ የወጡት፣ ሕወሓት የደቡብ ትግራይ አስተዳደራዊ መዋቅሮችን አፍርሶ በድጋሚ ለማደራጀት ማቀዱን የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል በቅርቡ ለወይን መጽሄት በሠጡት ቃለ ምልልስ መናገራቸውን በመቃወም ነው።

በተቃውሞ ሰልፉ ላይ”የራያ ህዝብ ድምፅ ይከበር፣ የደብረፂዮንን መግለጫ አጥብቀን እንቃወማለን፣ በመስዋዕትነት ስም ህዝብ መማገድ ይቁም” የሚሉ መፈክሮች ተስተጋብተዋል፡፡

ከትናንት ወዲያ በደቡብ ትግራይ የማይጨው ከተማ ነዋሪዎች፣ ተመሳሳይ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸው ይታወሳል።

(ዋዜማ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...