ሱዳን በጦርነቱ ዳፋ አንዳንድ ቤተሰቦች ሣር እየበሉ ነው

Date:

የሱዳን ጦር ሠራዊት (SAF) ካርቱም ከተማ የሚገኘውን ቤተመንግሥት በመቆጣጠር በሁለት ዓመቱ የርስ በርስ ጦርነት ወሳኝ የተባለውን ድል መቀዳጀቱ ተነገረ ። የሱዳን መንግሥታዊ ቴሌቪዥን ጦሩ ቤተመንግሥቱን ያስለቀቀው ከፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ (RSF) መሆኑን ዛሬ ማለዳ ዘግቧል ። ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ቤተመንግሥቱን ጨምሮ የሱዳን በርካታ ሰፈሮችን ለበርካታ ጊዜያት ተቆጣጥሮ ነበር ።

በሁለቱ የሱዳን ኃይላት መካከል ጦርነቱ ከዛሬ ሁለት ዓመት ግድም ማለትም (ሚያዝያ 7 ቀን፣ 2015 ዓ.ም) ከተቀሰቀሰ በኋላ ቤተመንግሥቱ ወዲያውኑ በፈጥኖ ደራሹ ኃይል ቁጥጥር ወድቆ ነበር ። ይህ ድል ለሱዳን ጦር ሠራዊት ታላቅ እመርታ እንደሆነ ቢገለጥም፤ ፈጥኖ ደራሹ ኃይሉ የካርቱም ደቡባዊ ክፍልን እና በዋና ከተማዪቱና ተጎራባቿ ኦምዱርማን ከተማ መካከል ያሉ ቦታዎችን አሁንም እንደተቆጣጠረ መሆኑ ተዘግቧል ።

ሁለት ዓመት በተጠጋው የሱዳን የርስ በርስ ጦርነት ከ28,000 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዘግቧል ።  ከሦስት ሚሊዮን በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል ። ጦርነቱ በፈጠረው ረሐብ የተነሳ አንዳንድ ቤተሰቦች በሕይወት ለመቆየት ሣር እየበሉ መሆናቸውን የፈረንሣይ ዜና አገልግሎት (AFP) ዘግቧል ። 

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...