በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

Date:

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን “American Space” ማዕከል በይፋ መርቀው ከፍተዋል።

በአሜሪካ ኤምባሲ ድጋፍ የተገነባው ማዕከሉ ለዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች፣ መምህራን፣ ተመራማሪዎች እንዲሁም ለአካባቢው ወጣቶች በምርምር፣ በቴክኖሎጂና በዲጂታል ክህሎት ዘርፍ የተለያዩ ነጻ አገልግሎቶችን ይሰጣል።

ማዕከሉ ፦
– የነጻ ኢንተርኔትና ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት፣
– በአሜሪካ የትምህርት ዕድሎች ላይ መረጃና ምክር፣
– በSTEM፣
– በኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣
– በሮቦቲክስ፣
– በዲጂታል ክህሎት እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ ስልጠናዎችን ያቀርባል።

በተጨማሪም በአመራር፣ በሙያ ክህሎት፣ በፈጠራ ሥራ እና በሚዲያ እውቀት ላይ ያተኮሩ ውይይቶችና ወርክሾፖች ይካሄዳሉ።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የሲዳማ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በየነ ባራሳ፣ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ እና ሌሎች የክልሉና የከተማው ከፍተኛ ኃላፊዎች ተገኝተው ነበር።

አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ ማዕከሉ ወጣቶችን በቴክኖሎጂና በምርምር ዘርፍ የሚያበረታታ መሆኑን ገልጸው፣ የአሜሪካ ኤምባሲ ድጋፉን እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የሲዳማ ክልልና የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኃላፊዎችም ማዕከሉ ለተማሪዎች፣ ለተመራማሪዎችና ለወጣቶች የዓለም አቀፍ የእውቀትና የክህሎት ዕድሎችን እንደሚያሰፋ ገልጸዋል።

@tikvahethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አዲስ ጦርነት ከተቀሰቀሰ ኢራን የበለጠ ምላሽ በመስጠት የተራዘመ ጦርነት እንደምታካሂድ አስታወቀች

ከፍተኛ የኢራን ወታደራዊ ባለሥልጣናት አሜሪካ ሌላ ዙር ጥቃት በአገራቸው...

ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ደርሷል

ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በሥራ ቡድን ደረጃ እየተካሄደ የሚገኘውን...

የጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ 28 የውጭ ዜጋ ተማሪዎችን ከኢትዮጵያውያን ቤተሰቦች ጋር ማስተሳሰሩን ገለጸ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በጎንደር ቃል-ኪዳን ቤተሰብ መርሃ-ግብር አማካኝነት በዘንድሮው ዓመት...

የሕግ ተማሪዎቹ አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...