በመቐለ ከተማ ከ17 ሺ ሊትር በላይ ነዳጅ በቁጥጥር ስር ዋለ

Date:

በመቐለ  ከተማ በሚገኙ 15 ነዳጅ ማደያዎች በቂ የነዳጅ አቅርቦት በማስገባት አገልግሎት እየተሰጠ የነበረ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ወደ ትግራይ ይገባ ነበረ ነዳጅ መቆራረጡን ተከትሎ በተፈጠረ የአቅርቦት ችግር ህገወጥ የነዳጅ ግብይትና ምርትን የመደበቅ ተግባራት መበራከታቸውን የመቐለ  ከተማ ምክትል ከንቲባ የሆኑ አቶ ኤልያስ ካህሳይ ገልፀዋል።

ምክትል ከንቲባው ይህን ተከትሎ በመቐለ  ከተማ አራት ክፍለ ከተሞች በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ 17 ሺ ሊትር በህገወጥ መንገድ የተከማቸ ነዳጅ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስታውቀዋል።

ከዚህ ባሻገር የመሰረታዊ ሸቀጦች የዋጋ ንረት በከተማይቱ ስለመኖሩም በቅኝት ማረጋገጣቸው የገለፁት አቶ ኤልያስ ያልተገባ ትርፍን ለማግኘነት የሚሹ ነጋዴዎች የአቅርቦት እጥረት በሌለበት ሁኔታ በምግብ ዘይትና በሌሎች መሰረታዊ ሸቀጦች የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ መኖሩንና ይህንን አድርገው በተገኙ ነጋዴዎች ላይም የንግድ ተቋም እስከማሸግ የሚደርስ እርምጃ መወሰድ መጀመሩን መናገራቸዉን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ በተመሳሳይ ሰው ሰራሽ የዋጋ ንረትና ምርትን በመደበቅ ስራ ተሰማርተው የተገኙ የአይደር፣ ዓዲ ሓቂ፣ ቀዳማይ ወያነና በኩሓ ክፍለ ከተማ በንግድ ስራ የተሰማሩ ስድስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸው የገለፁት ምክትል ከንቲባው ምርትን በመደበቅ የዋጋ ንረት እንዲፈጠር እያደረጉ ያሉትን ተከታትሎ በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ድንገተኛ ፍተሻዎቹ ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...