በሞሮኮ ዋና ከተማ በራባት በተደረገው ሰልፍ ላይ እስራኤል በጋዛ የምትፈፅመውን ጥቃት እንድታቆም ተጠይቋል።በሞሮኮ የሚንቀሳቀሰው ፍትህና እድገት ፓርቲ ፍልስጤማውያንን የሚደግፍ ለወራት የሚዘልቅ ግዙፍ ሰልፍ የጠራ ሲሆን ይህን ተከትሎም በአስር ሺዎች የሚቅጠሩ ሰልፈኞች ከበሮ እየመቱና ፍሊስጤማውያንን የሚደግፍ መፈክሮችን እያሰሙ በመሀመድ አራተኛ ጎዳና ላይ ሰልፍ አድርገዋል።
ሰልፈኞቹ የፍልስጤምን ባንዲራ ጨምሮ በእስራኤል የተገደለው የሀማሱ የፖለቲካ ሊቅ የያህያ ሲንዋርን ፎቶ ይዘው ታይተዋል። በሰልፉ ላይ ታዳጊዎች የተሳተፉ ሲሆን በጋዛ እየፈፀሙ ባሉ ጥቃቶች ለተገደሉት ህፃናት ማስታወሻነት የሚውል መሀሉ ላይ ቀይ ምልክት ያረፈበት ነጭ ባንዲራም ይዘው ተስተውለዋል።
በአሁኑ ሰዓት በጋዛ ውስጥ የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 50 ሺ የተሻገረ መሆኑን የጋዛ ጤና ሚኒስተር ያስታወቀ ሲሆን በሰልፉ ላይም ነፃነት የፈለገን ሰው መገደል የለበትም የሚል መፈክር ጎልቶ ተሰምቷል።ሰልፈኞቹ እኛ ነፃ ፍሊስጤምን እንፈልጋለንም ያሉ ሲሆን “በወንጀለኛው ኔታንያሁ በጋዛ ላይ የተጣለው ከበባ መቆም አለበት በአፋጣኝ የነፍስ አድን እርዳታ ወደ ጋዛ መግባት አለበት” ሲሉም ተደምጠዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ሰልፈኞቹ በአሜሪካ አመቻችነት እኤአ 2020 ዳግም የጀመረው የሞሮኮና የእስራኤል ግንኙነትም እንዲቋረጥ ጠይቀዋል።
@ዳጉ
