በሀገር ውስጥ አቅም ለመጀመሪያ ጊዜ በሶፍዑመር ዋሻ ላይ የተዘረጋው የባቡር መሥመር ስኬታማ የሙከራ ሥራ የተከናወነበት መሆኑን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አስታወቀ፡፡
የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ህሊና በላቸው በብሔራዊ የባቡር ቢዝነስና ኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ ከ100 ዓመት በላይ የባቡር ታሪክ ያላት ሀገር ብትሆንም በዘርፉ ዕድሜዋን ያገናዘበ ዕድገት አላስመዘገበችም።
ሆኖም አሁን ላይ በአዲስ መልክ በኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መሠረተ ልማቶች እየተሠሩ መሆኑን ጠቁመዋል።
በሀገር ውስጥ አቅም ለመጀመሪያ ጊዜ በሶፍዑመር ዋሻ ላይ የተዘረጋው የባቡር መሥመርም ስኬታማ የሙከራ ሥራ የተከናወነበት መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም እንደ ሀገር ትልቅ ስኬት መሆኑን አመላክተዋል።
ጋዜጣ_ፕላስ
