በበርበራ እና በአዲስ አበባ መካከል ቀጥታ በረራ በቅርቡ እንደሚጀመር ተጠቆመ

Date:

የሶማሌላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን ሞሐመድ አብዱላሂ የበርበራ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ጎብኝተዋል። በዚህ ወቅትም አየር ማረፊያው አሁን ላይ ለዓለም አቀፍ ንግድ ክፍት መሆኑን መሆኑ ተገልጿል።

የሶማሊላንድ የአቬሽን ሚኒስትሩ ፉአድ አህመድ ኑኡስ በበርበራ እና በአዲስ አበባ መካከል የካርጎ እና የመንገደኞች በረራ በቅርቡ እንደሚጀመር አረጋግጠዋል።

በዚህም በርበራን ከአዲስ አበባ ጋር በማስተሳሰር ሶማሊላንድ፥ የዓሳ እና ሌሎች ምርቶች በበርበራ ኤርፖርት ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ ያስችላታል ተብሏል።

በአዲስ አበባ እና በርበራ መካከል የሚደረገውን ጉዞ ቀላል በማድረግ የንግድ እና ቱሪዝምን እድገቱን ለማስፋትም ታቅዷል።

ዘገባው የሶማሊላንድ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...

“ሎዛ ዘፀአት”እና “የሎዛ ድርሳናት”ተከታታይ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍት ተመረቁ

በጋዜጠኛና ደራሲ መርዕድ እስጢፋኖስ የተጻፉት ሎዛ ዘፀአት(2014 ዓ.ም) እና...