ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የመቀለ ቅርንጫፍ የጽህፈት ቤት ሀላፊ የሆኑት አቶ ፀሀይ አምባዬ እንደተናገሩት ክልሉ በ2017 በጀት ዓመት 6 ዘር አፈፃፀም ተቋሙን የሚመለከት 29 አቤቱታወች መካከል 24 የሚሆነዉን መመለስቸዉንና 5 በሂደት ላይ እንደሉ ተናግረዋል።
ከቀረቡት የአቤቱታ መዝገቦች ውስጥ የመጀመሪያ ደረጃውን የሚይዙት የሥራ ማጣት፣ ከሥራ መባረር እንዲሁም ቅጥርን የሚመለከቱ አቤቱታዎች ሲሆኑ፤ በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ “አገልግሎት ማግኘት አልቻልንም” የሚሉ አቤቱታዎች መሆናቸውን ኃላፊው ተናግረዋል።
አሁንም ከተማዉ በሁለት ከንቲባ በመከፈሎ ምክንያት ህዝቡ መልስ የሚሰጠዉ አካል እያጠ እንደመጣ ተናግረዋል።
ሌሎች አቤቱታዎች የመሬት ይዞታና የጡረታ መብትን የሚጠይቁ መሆናቸውንና
በተለይም በክልሉ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞችና ተገልጋዮች በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ በርካታ ቅሬታ እንዳላቸው መስተዋሉን ተናግረዋል ።
የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም
