🔊 ስያሜው ኢትዮጵያን የቀጣናው የዕውቀት፣ የክህሎት ልማት እና የፈጠራ ማዕከል እንደሚያደርጋት የኢትዮጵያ ሜትሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታውቋል።
🌀 ይህ ውሳኔ የፀደቀው ሰኔ 15 በተካሄደው 80ኛው የዓለም ሜትሮሎጂ ድርጅት ሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ነው።
👉 ማሠልጠኛዎቹ በሜትሮሎጂ፣ ሃይድሮሎጂ እና የአየር ንብረት አገልግሎቶች ዘርፍ የሥልጠና እና የአቅም ግንባታ የልህቀት ማዕከላት ሆነው እንደሚያገለግሉ ኢንስቲትዩቱ በማኅበራዊ ገጹ ባጋራው መረጃ ገልጿል።
🌍 ይፋዊ እውቅናውን ተከትሎም ኢንስቲትዩቱ እና ዩኒቨርሲቲውየሥልጠና አገልግሎቶቻቸውን በሀገር አቀፍ፣ በቀጣናዊ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ማስፋፋትን ጨምሮ ወደ ሙሉ የትግበራ ሥራ እንዲገቡ ይጠበቅባቸዋል።
