በትግራይ ክልል የደሞዝ ክፍያ ተቋረጠ

Date:

በትግራይ ክልል የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች ለከፍተኛ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ መጋለጣቸው ተገልጿል።

የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ባወጣው ይፋዊ ደብዳቤ፣ የካቲት ወርን ጨምሮ ለቀጣይ ጊዜያት የሚውል የደሞዝ ክፍያ የሚሆን የጥሬ ገንዘብ እጥረት ማጋጠሙን አረጋግጧል።

ይህ “ላልተወሰነ ጊዜ” ይቆያል የተባለው የክፍያ መቋረጥ፣ በክልሉ ካዝና ውስጥ በቂ የገንዘብ ዝውውር  ባለመኖሩ እና ከፌዴራል መንግስት የሚጠበቀው የበጀት ድጋፍ በመዘግየቱ የመጣ እንደሆነ ተገልጿል።

ይህ ድንገተኛ ሁኔታ በተለይ የኑሮ ውድነት አሳሳቢ በሆነበት በዚህ ወቅት መከሰቱ፣ በሺዎች በሚቆጠሩ ሰራተኞችና በቤተሰቦቻቸው ህልውና ላይ ከባድ ስጋት ፈጥሯል።

የክልሉ መንግስት ለሁሉም ሴክተር መሥሪያ ቤቶች በላከው መመሪያ መሰረት፣ የደሞዝ ክፍያ ብቻ ሳይሆን የሥራ ማስኬጃ በጀቶችም ጭምር ተፅዕኖ እንዳረፈባቸው ታውቋል።

ሰራተኛው የዕለት ተዕለት ኑሮውን ለመምራት በሚታገልበት በዚህ ወቅት፣ የደሞዝ መቋረጥ ዜናው በክልሉ ያለውን ማህበራዊ ቀውስ ይበልጥ ሊያባብሰው እንደሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...