በአማራ ክልል የሚገኙ ተፈናቃዮች የምግብ እጥረት እንዳጋጠማቸው ገለጹ

Date:

በአማራ ክልል የሚገኙ ተፈናቃዮች የምግብና የመጠልያ እጥረት እንዳጋጠማቸው ተናገሩ፡፡

በሀገሪቱ በተለያዩ ክልሎች ግጭቶችና ጦርነቶች ሰበብ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በመጠለያ ጣቢያዎች ይገኛሉ፡፡

በክልሉ የደቡብ ወሎ፣ የሰሜን ጎንደርና የሰሜን ወሎ አንዳንድ ተፋናቃዮች ከጊዜ ወደ ጊዜ የእርዳታና የመጠለያ ችግር እያጋጠማቸው እንደሆነ መናገራቸውን ተዘግቧል፡፡ ከተፈናቃዮቹ መካከል የምግብ እርዳታ ካገኙ እስከ 5 ወራት እንደሆናቸው የተናገሩ ስለመኖራቸውም ተገልጿል፡፡

የክልሉ አደጋ መከላክልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን በበኩሉ የተፈናቃዮችን ችግር በዘላቂነት ለመመፍታት ጥረት እያደረገ መሆኑን የጠቀሰ ሲሆን፤ የምግብ እርዳታ ለማድርግ 500 ሚሊዮን ብር መድቦ እርዳታ እያቀረበ እንደሆነ ገልጿል፡፡

ኮሚሽኑ በክረምቱ ወቅት የጎርፍ ሥጋት ሊኖርባቸው ይችላል ተብለው በጥናት ለተለዩ አካባቢዎች ለአደጋ መከላከል ሥራ የሚውል 145 ሚሊዮን ብር መመደቡንም አመልክቷል፡፡

(ዶቼ ቬሌ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...