በአዲስ አበባ ከ75 እስከ 80 በመቶ ታክስ አሰባሰብ ግምት ላይ የተመሰረተ እደሆነ ተገለጸ

Date:

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ቢሮ  በከተማዋ ከ75 እስከ 80 በመቶ የታክስ አሰባሰብ ግምት ላይ የተመሰረተ እደሆነ ገልጿል፡፡

በቢሮው የታክስ ኦዲት ዳይረክተር አቶ ጌታቸዉ ግርማ፤ግብር ከፋዩ አሁን ላይ ግብሩን እየከፈለ ያለዉ የተደራጀ ሰነድ ይዞ ሳይሆን በግምት ነዉ ብለዋል፡፡

አቶ ጌታቸዉ  ብዙ ጊዜ ግምት ትክክል ሊሆን አይችልም ስለዚህም መንግስትንም  ሆነ ህዝብን ከህግ ውጭ የመጉዳትም የመጥቀምም አጋጣሚዎችን ሊፈጥር ይችላል ብለዋል፡፡

በአዲስ አበባም ሆነ የክልል የገቢዎች ቢሮዎችም አሁን ላይ የግብር የአሰባሰብ ስርዓታቸዉ፤በጥናት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን በግምት ላይ በመሆኑ ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ ስረአት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በመሆኑም ሁሉም ዜጋ ግዴታዉን አዉቆ ህጋዊ ሃላፊነቱን የሚወጣበት ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ ስርዓት በመዘርጋት ላይ እንዳለ አቶ ጌታቸዉ ግርማ አስታዉቋል፡፡

መጋቢ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ሰማያት ተከፈቱ ፣ ምስጢርም ተገለጠ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመዷ ቅድስት...

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...