በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ቢሮ በከተማዋ ከ75 እስከ 80 በመቶ የታክስ አሰባሰብ ግምት ላይ የተመሰረተ እደሆነ ገልጿል፡፡
በቢሮው የታክስ ኦዲት ዳይረክተር አቶ ጌታቸዉ ግርማ፤ግብር ከፋዩ አሁን ላይ ግብሩን እየከፈለ ያለዉ የተደራጀ ሰነድ ይዞ ሳይሆን በግምት ነዉ ብለዋል፡፡
አቶ ጌታቸዉ ብዙ ጊዜ ግምት ትክክል ሊሆን አይችልም ስለዚህም መንግስትንም ሆነ ህዝብን ከህግ ውጭ የመጉዳትም የመጥቀምም አጋጣሚዎችን ሊፈጥር ይችላል ብለዋል፡፡
በአዲስ አበባም ሆነ የክልል የገቢዎች ቢሮዎችም አሁን ላይ የግብር የአሰባሰብ ስርዓታቸዉ፤በጥናት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን በግምት ላይ በመሆኑ ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ ስረአት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
በመሆኑም ሁሉም ዜጋ ግዴታዉን አዉቆ ህጋዊ ሃላፊነቱን የሚወጣበት ዘመናዊ የታክስ አሰባሰብ ስርዓት በመዘርጋት ላይ እንዳለ አቶ ጌታቸዉ ግርማ አስታዉቋል፡፡
መጋቢ
