በውቅሮ ከተማ ወጣት ሊድያን የገደለዉ ግለሰብ ተፈረደበት

Date:



ከወራት በፊት በውቅሮ ከተማ የተፈፀመው የግድያ ወንጀል የበርካቶችን ልብ የሰበረ ነበር። ወጣት ሊዲያ አግብታ ለወግ ማረግ በቅታ ልጆችን አፈራበታለው ያለችው ትዳር ባልተጠበቀ ሁኔታ ህይወቷን አሳጥቷታል። ሰርጓ በተደግሰ በአራት ቀናት ልዩነት የህይወቴ አጋር የልጆቼ አባት ባለችው ሰው ግድያ እንደተፈፀመባት ተረጋግጧል።

የወጣት ሊድያ አለም ግድያ ተከትሎ  ዛሬ መጋቢት 25 ቀን 2017 በውቅሮ ከተማ የሚገኘውን የምስራቃዊ ዞን መካከለኛ ፍርድ ቤት ባዋለው ችሎት በወጣት ሊድያና ባለቤቷ መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የሟችን ሁለት አይኖች ከመሞቷ በፊት ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በማውጣት ጎሮሮዋን አንቆ እንደገደላት መረጋገጡን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።

በዚህ መሰረትም ፍርድ ቤቱ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ 539(1) ሀ መሰረት ተከሳሽ በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ብይን ሰጥቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከባድ ሙስና የተከሰሱትን 4 ተከሳሾችን፤ ፖሊስ ፍርድ ቤት ማቅረብ ሳይችል ቀረ

በከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው በፖሊስ የ'ይፈለጋሉ" ማስታወቂያ የወጣባቸው...

ስለመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ውጥረት እስካሁን የታወቁ ጉዳዮች

🔸 ትላንት ምሽት ከኢራን ግዛት የተተኮሰ የሮኬት ጥቃት በሰሜናዊ...

የወንጀል ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕጉ በጋዜጣ እስኪታተም ረቂቅ ሰነዶችን ከመጠቀም እንዲቆጠብ የፍትሕ ሚኒስቴር አሳሰበ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፍትሕ ሚኒስቴር አዲሱ የወንጀል ሕግ ሥነ-ሥርዓትና ማስረጃ ሕግ...

ፔንታጎን የእስራኤል ስለላ እንደሚያሳስበው ተገለጸ

ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ፔንታጎን እስራኤል ከፍተኛ ልዑኮችን ጨምሮ የአሜሪካ...