በውቅሮ ከተማ ወጣት ሊድያን የገደለዉ ግለሰብ ተፈረደበት

Date:



ከወራት በፊት በውቅሮ ከተማ የተፈፀመው የግድያ ወንጀል የበርካቶችን ልብ የሰበረ ነበር። ወጣት ሊዲያ አግብታ ለወግ ማረግ በቅታ ልጆችን አፈራበታለው ያለችው ትዳር ባልተጠበቀ ሁኔታ ህይወቷን አሳጥቷታል። ሰርጓ በተደግሰ በአራት ቀናት ልዩነት የህይወቴ አጋር የልጆቼ አባት ባለችው ሰው ግድያ እንደተፈፀመባት ተረጋግጧል።

የወጣት ሊድያ አለም ግድያ ተከትሎ  ዛሬ መጋቢት 25 ቀን 2017 በውቅሮ ከተማ የሚገኘውን የምስራቃዊ ዞን መካከለኛ ፍርድ ቤት ባዋለው ችሎት በወጣት ሊድያና ባለቤቷ መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የሟችን ሁለት አይኖች ከመሞቷ በፊት ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በማውጣት ጎሮሮዋን አንቆ እንደገደላት መረጋገጡን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።

በዚህ መሰረትም ፍርድ ቤቱ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ 539(1) ሀ መሰረት ተከሳሽ በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ብይን ሰጥቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አባቴ ለእኔ አባት ብቻ አልነበረም፤ ለእናቴ ታማኝ ባል፣ ለሁላችንም ደግሞ የደስታ ምንጭ ነበር

"አባዬ… ዛሬ ላለሁበት ማንነት መሰረት የሆንከኝ አንተ ነህ!" ​የአርቲስት...

የአንበሶቹ ትንሳኤ፦ የዳካር እንባ እና የቴራንጋ ድል

​በዳካር ሰማይ ስር ዛሬ ጨረቃ አልወጣችም፤ ይልቁንም በሚሊዮን የሚቆጠሩ...

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...

“ሎዛ ዘፀአት”እና “የሎዛ ድርሳናት”ተከታታይ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍት ተመረቁ

በጋዜጠኛና ደራሲ መርዕድ እስጢፋኖስ የተጻፉት ሎዛ ዘፀአት(2014 ዓ.ም) እና...