ከወራት በፊት በውቅሮ ከተማ የተፈፀመው የግድያ ወንጀል የበርካቶችን ልብ የሰበረ ነበር። ወጣት ሊዲያ አግብታ ለወግ ማረግ በቅታ ልጆችን አፈራበታለው ያለችው ትዳር ባልተጠበቀ ሁኔታ ህይወቷን አሳጥቷታል። ሰርጓ በተደግሰ በአራት ቀናት ልዩነት የህይወቴ አጋር የልጆቼ አባት ባለችው ሰው ግድያ እንደተፈፀመባት ተረጋግጧል።
የወጣት ሊድያ አለም ግድያ ተከትሎ ዛሬ መጋቢት 25 ቀን 2017 በውቅሮ ከተማ የሚገኘውን የምስራቃዊ ዞን መካከለኛ ፍርድ ቤት ባዋለው ችሎት በወጣት ሊድያና ባለቤቷ መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የሟችን ሁለት አይኖች ከመሞቷ በፊት ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በማውጣት ጎሮሮዋን አንቆ እንደገደላት መረጋገጡን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።
በዚህ መሰረትም ፍርድ ቤቱ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ 539(1) ሀ መሰረት ተከሳሽ በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ብይን ሰጥቷል።
