በውቅሮ ከተማ ወጣት ሊድያን የገደለዉ ግለሰብ ተፈረደበት

Date:



ከወራት በፊት በውቅሮ ከተማ የተፈፀመው የግድያ ወንጀል የበርካቶችን ልብ የሰበረ ነበር። ወጣት ሊዲያ አግብታ ለወግ ማረግ በቅታ ልጆችን አፈራበታለው ያለችው ትዳር ባልተጠበቀ ሁኔታ ህይወቷን አሳጥቷታል። ሰርጓ በተደግሰ በአራት ቀናት ልዩነት የህይወቴ አጋር የልጆቼ አባት ባለችው ሰው ግድያ እንደተፈፀመባት ተረጋግጧል።

የወጣት ሊድያ አለም ግድያ ተከትሎ  ዛሬ መጋቢት 25 ቀን 2017 በውቅሮ ከተማ የሚገኘውን የምስራቃዊ ዞን መካከለኛ ፍርድ ቤት ባዋለው ችሎት በወጣት ሊድያና ባለቤቷ መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የሟችን ሁለት አይኖች ከመሞቷ በፊት ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በማውጣት ጎሮሮዋን አንቆ እንደገደላት መረጋገጡን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።

በዚህ መሰረትም ፍርድ ቤቱ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ 539(1) ሀ መሰረት ተከሳሽ በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ብይን ሰጥቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...