በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ኪንሻሳ በደረሰ ከባድ የጎርፍ አደጋ የበርካታ ሰዎች ሕይወት አለፈ

Date:

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ዋና ከተማ ኪንሻሳ የጣለው ከባድ ዝናብ ከፍተኛ የሆነ የጎርፍ አደጋ በመከሰቱ 30 ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን ቤቶችና መንገዶች ወድመዋል። የክልሉ ጤና ሚኒስትር ፓትሪየን ጎንጎ የሟቾችን ቁጥር የተገለፀው ጊዜያዊ መሆኑን አፅንዖት በመስጠት ሊጨምር እንደሚችል አስጠንቅቀዋል። አስብዛኛው የሞት አደጋ ያጋጠመው በግንብ መደርመም ነው ሲሉም አክለዋል።

ወደ 17 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች የሚኖሩባትን ከተማ አቋርጦ የሚሄደው የንድጂሊ ወንዝ አርብ ምሽት ግስቡን በማፈራረስ ዋናውን ብሄራዊ መንገድ አጥለቅልቋል። አሽከርካሪዎች ለሰዓታት ታግተው የቆዩ ሲሆን አንዳንዶቹ ሌሊቱን ሙሉ በመኪናቸው ውስጥ አሳልፈዋል። የኪንሻሳ ነዋሪ የሆነችው ፓትሪሺያ ሚኮንጋ ለሮይተርስ የዜና ወኪል እንደተናገረችው “ትላንትና ምሽት ጓደኛዬን ለመቀበል ከአየር መንገዱ ወደ ቤት ስንመለስ መኪናው ውስጥ አደርን ምክንያቱም ምንም አይነት የመኪና ማቆሚያ ቦታ ስላልነበረ ነው” ስትል ተናግራለች።

በርካታ ሰፈሮች የኤሌክትሪክ ኃይል በመቋረጡ በጨለማ ውስጥ ለማሳለፍ ተገደዋል። ሌሎች ደግሞ በውሃ እጥረት እየተቸገሩ ይገኛል። የኪንሻሳ ገዥ ዳንኤል ቡምባ ሉባኪ የውሃ መሠረተ ልማት ተጎድቷል ነገር ግን አቅርቦቱ በቀናት ውስጥ እንደሚመለስ ለነዋሪዎች አረጋግጠዋል። በመንግስት ቴሌቪዥን ላይ በሰጡት መግለጫ ለሞቱት ሰዎች ህገ-ወጥ ቤቶችን ተጠያቂ ያደረጉ ሲሆን ባልታቀደ ሰፈራ የሚኖሩ ሰዎች ከመኖሪያ ስፍራቸው ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!! በክርስቲያኖች ዘንድ ጥምቀት...

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...

ንግድ ባንክ “ስታርፔይ” የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ሥርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ቀልጣፋ...