እጅጋየሁ ታዬ ሻምፒዮን ሆነች

Date:

በጃማይካ ኪንግስተን በተደረገው የ5 ሺህ ሜትር ረጅም ርቀት ግራንድ ስላም ትራክ አትሌት እጅጋየሁ ታዬ በበላይነት አጠናቃለች።

14 ደቂቃ 54.88 ሰከንድ እጅጋየሁ ርቀቱን ለማጠናቀቅ የወሰደባት ጊዜ ሆኗል።

ቀደም ብላ የ3 ሺህ ሜትር ረጅም ርቀትን በተመሳሳይ በአንደኝነት ያጠናቀቀችው አትሌቷ
ያገኝችውን ነጥብ 24 በማድረስ የርቀቱ ሻምፒዮን ሆናለች።

በመሆኑም በአዲሱ ውድድር የአለም ሻምፒዮና የነሀስ ሜዳልያ ባለቤቷ አትሌት እጅጋየሁ ታዬ የ100 ሺህ ዶላር ተሸላሚ ሆናለች።

ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ጽጌ ገብረሰላማ 3ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።

ጽጌ በ3 ሺህ ሜትር ረጅም ርቀት በተመሳሳይ 3ኛ ሆና ማጠናቀቋ የሚታወስ ሲሆን ያገኝችውን ነጥብ 12 በማድረስ የ30 ሺህ ዶላር ተሸላሚ ሆናለች።

ኬንያዊቷ አግነስ ኒጌቲች ደግሞ በአጠቃላይ የረጅም ርቀት ውጤት 2ኛ ወጥታለች።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...