በጋዛ በረሃብና በተመጣጠነ ምግብ እጦት የ147 ሰዎችን ህይወት ተቀጥፏል

Date:


በጋዛ ቢያንስ 14 ፍልስጤማውያንና ሁለት ህፃናትን ጨምሮ በቅርቡ በረሃብና በተመጣጠነ ምግብ እጥረት ምክንያት ህይወታቸው ማለፉን የጤና ባለስልጣናት ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል ።

ይህ አሳዛኝ ክስተት እስራኤል በጥቅምት 2023 ጦርነት ከጀመረች ወዲህ በተመጣጠነ ምግብ እጥረት የሞቱት ሰዎች ቁጥርን ወደ 147 እንዲያድግ አድርጓል፤ ከእነዚህ ውስጥም  88ቱ ህፃናት መሆናቸው ነው የተነገረው ።

ይህ አስከፊ ዜና የወጣው የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በተከበበችው ጋዛ ግዛት “እውነተኛ ረሃብ” እየታየ መሆኑን ከገለጹ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ነው።

የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ከሁለት ቀን በፊት ባወጣው መግለጫ፣ በጋዛ ውስጥ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ምጣኔ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አስጠንቅቋል። በተለይም በሐምሌ ወር ብቻ የሞቱ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል ነው ያለው ድርጅቱ ።

ዩኒሴፍ በበኩሉ ባወጣው ሪፖርት፣ በጋዛ ያሉ ህፃናት “በረሃብ እየሞቱ” መሆናቸውን ገልጿል። ከሚያዝያ ወር ጀምሮ በተመጣጠነ ምግብ እጥረት የሞቱ ህፃናት ቁጥርም ከ52 ወደ 80 ከፍ ብሏል። ይህም ሦስት ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ የ54 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን አልጄዚራ ዘግቧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጥምቀት በዓል በመላ ሀገሪቱ በድምቀት እየተከበረ ነው

የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እና በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት...

“ሎዛ ዘፀአት”እና “የሎዛ ድርሳናት”ተከታታይ ረጅም ልቦለድ መጻሕፍት ተመረቁ

በጋዜጠኛና ደራሲ መርዕድ እስጢፋኖስ የተጻፉት ሎዛ ዘፀአት(2014 ዓ.ም) እና...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አደረሳችሁ፣ አደረሰን!! በክርስቲያኖች ዘንድ ጥምቀት...

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...