ቮዳኮምና ስታርሊንክ በአፍሪካ ኢንተርኔትን ለማስፋፋት ተስማሙ

Date:

ሁለቱ ተቋማት በአፍሪካ የገጠራማ አካባቢዎች የኢንተርኔት ተደራሽነትን ለማስፋትና ለቢዝነሶች ፈጣን ኢንተርኔት ለማቅረብ የሚያስችል ስምምነት ፈፅመዋል።

በስምምነቱ መሰረት የስታርሊንክ የሳተላይት ኢንተርኔት አገልግሎት በቮዳኮም የሞባይል ኔትዎርክ በኩል ሲሰጥ በገጠራማ አካባቢዎች ለሚገኙ ትምህርት ቤቶችና የጤና ተቋማት ፈጣን አገልግሎት መስጠት ያስችላል።

በተጨማሪ ቮዳኮም የስታርሊንክን መሳሪያዎች እና አገልግሎቶች በአፍሪካ ለሚገኙት ቢዝነሶች የመሸጥ መብት ተሰጥቶታል።

ቮዳኮም በ2030 የደንበኞቹን ቁጥር 260 ሚሊየን ለማድረስ እየሰራ ሲሆን ስምምነቱ ይኸንን ራዕይ እንዲያሳካ ያግዘዋል።

ስታርሊንክ በ25 የአፍሪካ ሃገራት እየሰራ ሲሆን ስምምነቱ ሌሎች አዳዲስ ተጠቃሚዎችን እንደሚጨምርለት ታምኖበታል።

@TikvahethMagazine

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...