ተወዳጇ የፊልም ባለሙያ እና የሰብአዊ ድጋፍ አቅራቢ የሆነችዉ የሆሊውድ ፈርጧ አንጀሊና ጆሊ በዛሬው ዕለት ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልን መጎብኘቷ ተነገረ።
ተዋናይቷ ባደረገችው ጉብኝት በዋነኝነት ሆስፒታሉ እየሰጠ በሚገኘው መድሃኒቱን የተላመደ ቲቢ (ኤም.ዲ.አር ቲቢ) ህክምና ዙሪያ እየተከናወኑ ያሉ እንቅስቃሴዎችን ፣ የሚታዩ ለውጦችን እንዲሁም ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ቦታዎች መለየት ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር።
በጉብኝቱ ላይ አንጀሊና የሆስፒታሉን የቲቢና መድሃኒቱን የተላመደ ቲቢ (ኤም.ዲ.አር ቲቢ) ህክምና አገልግሎት መስጫ ዋርድ ፣ ላብራቶሪ እንዲሁም ታካሚዎችን መመልከቷም ተገልጿል ።
አንጀሊና ወደ ሆስፒታሉ ከረጅም ጊዜያት በፊት መጥተታ እንደነበር በማስታወስ በአሁኑ ጉብኝቷ ላይ ሆስፒታሉ ዘርፈ ብዙ ለውጦች አምጥቶ መመልከቷ እጅግ ደስተኛ መሆኗን ተናግራለች ።
አክላም ሆስፒታሉ ድጋፍ ቢደረግለት በቀጣይ የተሻለ አገልግሎት ለታካሚዎች መስጠት በሚያስችለው አስተማማኝ ደረጃ ላይ እንዳለ በጉብኝቱ ላይ መገንዘቧን ገልፃለች ገልፀዋል።
በተጨማሪም በሆስፒታሉ በቲቢ ህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ የተገኘው እድገት በእጅጉ የሚደነቅ እና የሚያስተማምን ስለሆነ በቀጣይ በጂ.ኤች.ሲ (Global Health Committee (GHC)) በኩል ድጋፍ እናደርጋለን ብላለች።
/ቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል /
ተዋናይት አንጀሊና ጆሊ በሆስፒታሉ ጉብኝት አደረገች
Date:
