ቱርክ በሶማሊያ የመጀመሪያውን የባህር ላይ የነዳጅ ቁፋሮ ልትጀምር ነው

Date:

በሶማሊያ ታሪክ የመጀመሪያው የሆነውን የባህር ላይ የነዳጅ ቁፋሮ ፕሮጀክት ለመጀመር የሚያስችል የቱርክ የቁፋሮ መርከብ ዓርብ ዕለት በሞቃዲሹ ወደብ መድረሱ ተገልጿል።

ቻግሪ ቤይ የተሰኘችውና የቱርክን ሰንደቅ ዓላማ ያነገበችው ይህች ግዙፍ መርከብ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል በ2024 የተፈረመውን የሃይድሮካርቦን ልማት ስምምነት ተፈጻሚ ለማድረግ የመጣች ሲሆን፤ ስምምነቱ ለቱርክ የመንግሥት የነዳጅ ኩባንያ እያንዳንዳቸው 5,000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ባላቸው ሦስት የባህር ክልሎች ላይ የፍለጋ እና የቁፋሮ መብት ይሰጣል።

በ2024 መጨረሻ ላይ በተካሄደው የሴይስሚክ ጥናት መሠረት የሚከናወነው ይህ ሥራ፣ ለሶማሊያ የመጀመሪያው የባህር ላይ ቁፋሮ ሲሆን ለቱርክ ደግሞ ከራሷ የባህር ክልል ውጪ የምታካሂደው የመጀመሪያው ጥልቅ ባህር ላይ የሚደረግ የቁፋሮ እንቅስቃሴ ነው።

የቱርክ ኢነርጂ ሚኒስትር አልፓርስላን ባይራክታር እና የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ በተገኙበት በሞቃዲሹ ወደብ የክብር ሥነ-ሥርዓት የተከናወነ ሲሆን፣ ይህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጠንካራ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትብብር ወደ አዲስ የኃይል ልማት ምዕራፍ የሚያሸጋግር መሆኑ ተመልክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...